ቅዱስ ጊዮርጊስ 2-0 ሲዳማ ቡና
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሁለት ድል እልባ ጨወታዎች በኃላ ወደ እሸናፊነት የተመለሰበትን ድል አስመዝግቧል።በሜዳው አዲስ እበባ ስታድየም ሲዳማን ያስተናገዱት ጊዮርጊሶች በኢሱፍ ብርሃነ ና እቡበከር ሳኒ ሁለት ግቦች ታግዞ ሙሉ ሥስት ነጥብን እሳክቷል።ድሉን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 33 ሲያደርስ ሲዳማ ቡና ሁለተኛ ደረጃን ለፋሲል ከነማ እስረክቧል።

ደደቢት 2-3 ድሬዳዋ ከተማ
እምስት ግቦችን ያስተናገደው የደደቢት ና ድሬዳዋ ጨዋታ በእንግዶቹ ድሬዳዋ እሸናፊነት ተጠናቋል።የድሬዳዋ ሥስት የእሸናፊነት ግቦች ዘነበ ከበደ ና ረመዳን ናስር በመጀመርያው እጋማሽ ፍሬድ ሙሺንዲ በሁለተኛው እጋማሽ አስቆጥረዋል።የደደቢት ሁለት ግቦች የእብስራ ተስፋዬ በፍፁም ቅጣት ምት መድሃንየ ታደሰ በጨዋታ እስቆጥረዋል።
ፋሲል ከነማ 1-1 ደቡብ ፖሊስ
በሜዳቸው ፋሲለደስ ስታድየም ደቡብ ፖሊስን ያስተናገዱት ከመሪው መቐለ 70 እንደርታ ያላቸውን የነጥብ ልዩነት የማጥበብ እድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል።በሙጂብ ቃሲም ግብ መምራት የቻሉት ፋሲሎች ከ10 ደቂቃ በኃላ በሄኖክ እየለ እማካኝነት ደቡብ ፓሊሶች አስቆጥረው ጣፋጭ እንድ ነጥብ ይዘው ወጥተዋል።

ጅማ እባጅፋር 2-0 ስሑል ሽረ
በሜዳቸው ስሑል ሽረን ያስተናገዱት ጅማ እባጅፋር በኦኪኪ ኦፎላቢና እስቻለው ግርማ ግቦች ማሸነፍ ችሏል።በሁለተኛው ዙር መሻሻልን እያሳዩ ሚገኙት ጅማዎች ድሉን ተከትለው ነጥባቸውን 31 በማድረስ ስድስተኛ ደረጃን ይዘዋል።

አዳማ ከተማ 1-2 ሀዋሳ ከተማ
ከእሰልጣኛቸው ጋር የተለያዩት እዳማዎች በሜዳቸው ሽንፈትን እስተናግደዋል።እንግዶቹ ሃዋሳዎች በምንተስኖት እበራ ደስታ ዮሐሀንስ ግቦች ታግዘው መሉ ሥስት ነጥብን እሳክተዋል።የአዳማን ከባዶ ሽንፈት ያዳነች ግብ ቡልቻ ሹራ አስመዝግቧል።
ደስታ ዮሐንስ ለሀዋሳ ያስቆጠራት ጎል በተንቀሳቃሽ ምስል ይመልከቱ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቡልቻ ሹራ ለአዳማ ያስቆጠረውን ጎል
ጎል በተንቀሳቃሽ ምስል ይመልከቱ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ወላይታ ድቻ 2-1 ኢትዮጵያ ቡና
ወላይታ ድቻ በሜዳቸው ቦዲቲ ስታድየም ኢትዮጵያ ቡናን እስተናግደው በፀጋዬ እበራ ሁለት ግቦች ታግዘው ከወራ ቀጠናው እንዲርቁ ያገዛቸውን ድል አስመዝግበዋል።በእልሃሰን ካሉሻ ግብ እቻ መሆን ችለው የነበሩት ቡናዎች ውጤታቸውን ማስጠበቅ ሳይችሉ ቀርተዋል።
አስተያየት ይስጡ