መነሻ ገጽ Covid-19 የአፍሪካ እግር ኳስ እና ወቅታዊው ኮሮና ቫይረስ !
Covid-19አፍሪካዜናዎች

የአፍሪካ እግር ኳስ እና ወቅታዊው ኮሮና ቫይረስ !

አጋራ
አጋራ

 

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከዓለም አልፎ አፍሪካ ላይ ከተጋረጠ ወራቶችን ሲያስቆጥር እግር ኳሱ ላይ የራሱን አሻራ እያሳረፈ ይገኛል ::

በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሊግ በገንዘቡ ረገድ ተዳክመው ሲታዪ ሀገራችን ኢትዮጵያ በዘርፉ ከሚጠቀሱ ሀገራት ተርታ ትሰለፋለች :: ይህ ወረርሽኝ ከ አስራ ሰባት ሀገራት በላይ ሊጎቻቸውን እንዲያቋርጡ ሲያስገድድ እንደ ታንዛኒያ ፣ ቡሩንዲ እና ሶማሊያ ሊጋቸውን በማካሄድ ላይ ሲገኙ ግብፅ እና ሞሮኮን ጨምሮ ጥቂት ሀገራት ሊጋቸውን ዳግም ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ ::

የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ብሩንዲ ሊጓን በማካሄድ የዘንድሮውን የውድድር ዓመት ያጠናቀቀች ቀዳሚዋ ሀገር ለመሆን ችላለች ::

በዚህ ወረርሽኝ የሊጉ ክለቦች እና ተጫዋቾች በስፋት እየተጠቁባቸው ከሚገኙ ሀገራት ወስጥ ግብፅ እና ደቡብ አፍሪካ ዋነኞቹ ናቸው ::

ለአብነት ያክል የደቡብ አፍሪካው ሊግ በቀድሞው አጠራሩ አብሳ ፕርሚየር ሺፕ ይፋ በሆኑ እና በተረጋገጡ መረጃዎች ሁለት ተጫዋቾች መያዛቸውን ይፋ አድርገዋል ::

1. ጊቭን ማሺኪኒያ :- ብሎም ፋውንቴን ሴልቲክ ክለብ እየተጫወተ የሚገኘው የመሀል ሜዳው ተጫዋች ጊቭን ማሺኪኒያ በቫይረሱ መያዙ ከሶስት ቀናት በፊት ክለቡ ይፋ አድርጓል ::


2. ቤን ሞትሽዋሪ :- የኦርላንዶ ፓይሬትስ የመሀል ሜዳ ተጫዋች የሆነው ቤን ሞትሽዋሪ ከወራት በፊት ቫይረሱ እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን አሁን ላይ ሙሉ ለሙሉ ማገገሙን ክለቡ በማህበራዊ ድህረገጹ አሳውቋል ::

የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ግብፅ ሊጓን ዳግም ለማካሄድ ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ የሊጉ ክለቦች የቫይረሱን ምርመራ እንዲያደርጉ ሲያስጠነቅቁ በተደረገላቸው ምርመራ ስድስት ተጫዋቾች ከአራት ክለብ መያዛቸው ይፋ ሲደረግ አራቱ ክለቦችም ሱሞሀ ፣ ( ENPPI) ፣ ኢቲሀድ አሌክሳንድሪያ እና አል ሞክዋለን መሆናቸው ተግልጿል ::

የግብፅ ሊግ መጀመሩን ከተቃወሙ ክለቦች ውስጥ ቀዳሚው የሆነው በአወዛጋቢው ፕሬዝዳንት መንሱር ማንቶርዳ የሚመራው ዛማሌክ ክለብ ሲሆን ከደቂቃዎች በፊት ግብ ጠባቂያቸው ሞሀመድ አዋድ መያዙን የግብፅ መገናኛ ብዙሃን ክለቡን ዋቢ አድርገው ዘግበዋል ::

ይፋ በሆኑ መረጃዎች ይህ ፁሁፍ እስከ ተጠናከረበት ድረስ ከአስራ ሶስት በላይ ተጫዋቾች ሲያዙ የግብፅ ሶስተኛው ዲቪዝዮን ክለብ ባድራ የ 59 አመት የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ አብዶ በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ማለፉ የተገለፀ ብቸኛው የስፖርቱ አለም ግለሰብ ናቸው ::

ሊጎችን ዳግም ለማስቀጠል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በአንዳንድ ሀገራት ቢኖሩም ካፍ በመጪው ማክሰኞ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ ሲያካሂድ የአፍሪካ ዋንጫን ጨምሮ በስሩ ያሉ ውድደሮች ላይ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ይጠበቃል ::

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...