መነሻ ገጽ ዜናዎች የአሸናፊ በጋሻው የምስጋናና የዕውቅና መርሃግብር ተካሂዷል
ዜናዎች

የአሸናፊ በጋሻው የምስጋናና የዕውቅና መርሃግብር ተካሂዷል

አጋራ
አጋራ

 

በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ለዚህ ፕሮግራም አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢት.እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ኃይለየሱስ ፍሰሃ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ የኢትዮጲያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት የቀድሞ የዋሊያዎቹ አለቃ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ አቶ ኢሳያስ እንዳሉት ” ያልተለመደ ነገር እያደረጋችሁ ነው …አሸናፊ የተጫወተው ለኢትዮጲያ ቡና ኮሚቴው ግን እነ አቶ ኢሳያስ የኤሌክትሪክ እግር ኳስ ሃላፊ ነው እነ አንዋርም ሌሎቻችሁም ጥሩ ስራ ሰርታችሁዋልና ከመሳሳብ ወጥተን ለተሻለ ስራ የሚስበንጊዜ ላይ እንዳለን አሳይቶኛልና ደስተኛ ሆኛለሁ” ሲሉ ገልጸዋል፡፡ አሸናፊ በጋሻው ለኢትዮጲያ ቡና 12 አመት ሲጫወት የማሊያው ቁጥር 12 መሆኑ ግጥምጥሞሹን የተለየ አድርጎታል፡፡ የኢት.ቡናው የቦርድ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ኮሚቴውን አመስግነዋል፡፡” የአሸናፊን የቡና ተሳትፎ በዚህች ጊዜ መናገር አይቻልም ከC እስከ A ተሰልፎ ተጫውቷል የክለቡ ነብር ማለት ነው ደጋፊውን በታላቅ ወኔ ሲመራ የነበረ ተጨዋች ነው ሽንፈትን በፍጹም አይቀበልም አንድ ታሪክ ልንገራችሁ አንዴ ከምድርጦር ጋር እየተጫወትን 2ለ1 መሩን ብንሞክር ብንሞክር ግብ እንቢ አለን አሸናፊ ግን ረብሻ ፈጠረና ጨዋታው ተቋረጠ፡፡ አሰልጣኝ ስዩም አባተ ጋር ሄድኩና ለምንድነው አሸናፊ ረብሻ ያነሳው ስለው አታውቀውም እንዴ እሱኮ ሽንፈት አይወድም አለኝ ይሄ ነው አሸናፊ”በማለት አሞግሰውታል፡፡

“በአንድ ወቅት በተፈጠረ ችግር ክለባችን ደመወዝ መክፈል አልችል ሲል ሁሉም ተጨዋቾች ወደሌላ ክለብ ሲሄዱ አሸናፊ ግን ቡናን አልለቅም ቡና በችግር መመለስ ካልቻለ እኔም አልመለስም እንጂ የማንንም ደጅ አላንኳኳም ያለ ጀግናችን ነው አሸናፊ 12 ቁጥር ማሊያ ሲለብስ ኖሯል አሁንም ይህን ቁጥር ለደጋፊዎቻችን ስንሰጥ በሁሉም ልብ ውስጥ እንዳለ ርግጠኞች ነን በቀጣይም ተመሳሳይ ፕሮግራም ይኖረናል ” በማለት ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል፡፡ ፕሮግራሙ ቀጥሏል.. ክለቡ የደጋፊ ማህበሩ ሽልማት ሰጥተውታል፡፡ ኮሚቴውም 2 ወራት ከሰራ በኋላ የተሰበሰበውን 905 ሺ ብር ለአሸናፊ በጋሻው አበርክተውለታል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...