መነሻ ገጽ Covid-19 የቅዱስ ጊዮርጊስና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ስታድየም አካባቢ ለሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ድጋፍን አደረጉ-ምሳም አበሉ
Covid-19ዜናዎች

የቅዱስ ጊዮርጊስና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ስታድየም አካባቢ ለሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ድጋፍን አደረጉ-ምሳም አበሉ

አጋራ
አጋራ

በአዲስ አበባ ስታድየም የሚታደሙ የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች እንደዚሁም ደግሞ የእነሱም የቅርብ ጓደኞች ኮሮና ቫይረስን በጋራ ለመከላከል ይቻል ዘንድ በትናንትናው ዕለት ለበርካታ የጎዳና ተዳዳሪዎች ቫይረሱን ሊከላከሉ የሚችሉበትን የማክስ እና የሳሙና ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር የምሳ ማብላት ፕሮግራምንም አድርገዋል።


የአዲስ አበባ ስታድየም ላይ በነበረው የትናንቱ ልዩ ፕሮግራም ላይ እስከ 350 ለሚደርሱ የጎዳና ተዳዳሪዎች በነበረው የምሳ ማብላት ፕሮግራም ላይ ኮሮና ቫይረስን እንዴት መከላከል እንደሚቻል የግንዛቤ ማስበጫ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ይህ ፕሮግራም የተዘጋጀበት ዋና ዓላማም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለጎዳና ተዳዳሪዎች እንደሌላው ማህበረሰብ በአሁን ሰዓት ማን አለላቸው በሚል ከእነሱ ጎን ለመቆም እንደሆነና በዕለቱም ከሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች የተሰባሰበው የገንዘብ እርዳታም ገቢው ለእነዚህ የጎዳና ተዳዳሪዎች ሆኖ የመጪውን የፋሲካ በዓል በሌላ ልዩ ፕሮግራም እንዲያሳልፉበት እንደሚደረግ ተገልጿል።


የቅዱስ ጊዮርጊስና የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከያ ባዘጋጁት ፕሮግራም ላይ ሁሌም በእንደዚህ አይነት ዝግጅት ላይ በመታደም የሚታወቀው ድምፃዊ ያሬድ ነጉ በክብር እንግድነት የተገኘ ሲሆን ከእሱ ውጪም በቦክስ ስፖርት ተወዳዳሪነታቸው ከዚህ ቀደም ይታወቁ ከነበሩት ውስጥ ታዋቂው ቦክሰኛ ፀጋስላሴ አረጋዊ ኮሮኮንች እና እንደዚሁም ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሀላፊዎች መገኘታቸው ታውቋል።


በመጨረሻም ይህ ፕሮግራም ሲጠናቀቅ ለእነዚህ ጎዳና ተዳዳሪዎች ማን አላቸው በሚል የገንዘብ እርዳታና ድጋፍ ላደረጉት የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች እና በፕሮግራሙ ላይ ለታደሙት ሌሎች አካላትም ከአዘጋጆቹ ከፍተኛ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...