የመጀመሪያዋ ባለቀለምና ተወዳጇ ሀትሪክ ሳምንታዊ የስፖርት ጋዜጣ በቅድሚያ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን፣ ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለች እንደተለመደው አዳዲስና ትኩስ ዘገባዎችን አካታ በገና በዓል ምክንያት ከነገ በስቲያ ማለዳ እጅዎ ትገባለች ይጠብቋት።
ሀትሪክ ስፖርት ከነገ በስቲያ እትሟ የኢትዮጵያ ቡናውን ተከላካይ ፈቱዲን ጀማልን በተወዳጅና በርካታ ተከታታዮች ባሉት The Big Interview አምዷ ይዛ ትቀርባለች።
የሀትሪክ ጋዜጣ ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተር የሆነው ጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ ከኢትዮጵያ ቡናው ተከላካይ ጋር በነበረው ቆይታ “ለኢትዮጵያ ቁና የፈረምኩት የቡድኑ አጨዋወት እና በቃላት የማይገለፀው ደጋፊ አደጋገፍ ማርኮኝ ነው።” ብሏል። ስለ አዲሱ የኢትዮጵያ ቡና አጨዋወት የተጠየቀው ተከላካዩ “አትጠራጠሩ የካሳዬ ፍልስፍና ከክለብ አልፎ ለሀገር የሚጠቅም ነውና ታገሱን።” በማለት መልስ ሰጥቷል። ከዚህ በተጨማሪም ስለ ኮከብነቱ የተጠየቀው ፈቱዲን “ኮከብ ተጫዋች መባሌ ከመኩራራት ይልቅ ከባድ ኃላፊነት ጥሎብኛል።” ሲል ምላሽ ሰጥቷልና የረቡዕ ዕትም እንዳያመልጣችሁ።
በሌላ የሀገር ውስጥ ዘገባ በቅዳሜው እና እሁዱ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዙሪያ ምን ተባሉ የሚሉ እና ሌሎች ዜናዎችንም አካተናል። ሙሉ ዘገባውን ረቡዕ ሀትሪክ ላይ ያነቡታል።
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዋስ ምን ታስነብቦት ይሆን? ስለማያረጀው ዝላታን ኢብራሂሞቪች ዙርያ የተጠናከረ ልዩ ዘገባን ይዛለች፤ የአርሰናሉ ተከላካይ ሶክራተስ ፓፓስቶፖሎስ ከዩናይትዱ ድል በኋላ የሰጠው ምላሽ በሀትሪክ ተካቷል፣ ከእሱ በተጨማሪ የሊቨርፑሉ አንዲ ሮበርትሰን፣ የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቧ ኩረቷ ቃለ-ምልልስና ሌሎች ዘገባዎች ተካዋል። የረቡዋ ሀትሪክ ሌላም የሚወዱትን ዘገባ ይዛሎት ቀርባለች፡፡ ሀትሪክ አታምልጦት፡፡
የሀትሪክ ስፖርት የረቡው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል።
ሀትሪክን ከጋዜጣዋ በተጨማሪ በድረ-ገፅዋ hatricksport.net አዳዲስ መረጃዎችን ያገኛሉና ዛሬውኑ ይጎብኙን።
በድጋሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ ምኞታችን ነው።
አስተያየት ይስጡ