ወላይታ ድቻ እግር ኳስ ቡድን በቀጣዩ አመት ላለበት የኢንተርናሽናል የኮንፌዴሬሽን ጨዋታ ተጫዋቾችን በማሰፈርመ ላይ ይገኛል፡፡
በያዝነው አመት ለሀዋሳ ከተማ ትልቅ ግልጋሎትን የሰጠው ጃኮ አራፋትን ማስፈረም ችሏል፡፡
ጃኮ አራፋት በ2009 የኢትዮጵያ ፕሪሜየር ሊግ ለሀዋሳ ከተማ 12 ግቦችን ማስቆጠሩ እሚታወስ ነው፡፡
ሌላው ለክለቡ የፈረመው በሀዲያ ሆሳዕና ሁለት አመታትን ማሳለፍ የቻለው አመረላ ደልታታን ከሀዲያ ሆሳዕና በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ እሚመራው ወላይታ ድቻ በይፋ ማስፈረም ችሏል፡፡

አስተያየት ይስጡ