መነሻ ገጽ ዜናዎች ዜና | ጌታነህ ከበደ በወላይታ ድቻው ጨዋታ ይሰለፋል።
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግደደቢት

ዜና | ጌታነህ ከበደ በወላይታ ድቻው ጨዋታ ይሰለፋል።

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ(መጋቢት 15 እና 16 2010ዓ.ም) አ/አ ላይ እና በክልል ስታዲየሞች ላይ በሚደረጉ ጨዋታዎች ጅማሬውን የሚያደርግ ይሆናል።

ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል እሁድ በብቸኝነት የሚስተናገደው የወላይታ ድቻ እና የደደቢት ጨዋታ ተጠቃሽ ነው። በዚህም ጨዋታ ላይ በቅጣት ለ3 ጨዋታዎች ከሜዳ ርቆ የነበረው ጌታነህ ከበደ ወደሜዳ የሚመለስ ይሆናል። ጌታነህ በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ዙር 13ኛ ሳምንት ላይ ክለቡ ደደቢት ጅማ አባጅፋርን አስተናግዶ 2-1 በተሸነፈበት ጨዋታ ላይ ከጨዋታ ውጪ የተጋጣሚን ተጫዋች በክርኑ በመማታት በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቶ የ4ጨዋታዎች ቅጣት ተጥሎበት እንደነበር የሚታወስ ነው። ሆኖም ክለቡ ደደቢት ተጫዋቹ 3ጨዋታዎች መቀጣቱን በማስታወስ አራተኛው ጨዋታ ቅጣት እንዲነሳለት ይግባኝ አስገብቶ ይግባኙ በፌዴሬሽኑ ተቀባይነት በማግኘቱ ቅጣቱ ተነስቶለት ለዕሁዱ ጨዋታ የመጫወት ፈቃድ አግኝቷል።

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 3ጨዋታዎችን የተቀጣው ጌታነህ ከበደ ከጅማ አባጅፋሩ ኦኪኪ አፎላቢ ጋር የሊጉን ኮከብ ግብ አግቢነት በ9 ግቦች በጋራ እየመራ ይገኛል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...