በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 12ኛው ሳምንት ባሳለፍነው ቅዳሜ እና ዕሁድ(ጥር 12 እና 13 2010ዓ.ም) አ/አ ላይ ሊደረጉ የታሰቡት አራት ጨዋታዎች (ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ፣ ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ከ ድሬዳዋ ከተማ፣ መከላከያ ከ መቐለ ከተማ እና ቅ/ጊዮርጊስ ከ ደደቢት) በቂ የፀጥታ ሀይል ባለመኖሩ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘማቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
ሆኖም ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን የውድድር እና ስነ ስርዓት ኮሚቴ ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት እነዚህ ጨዋታዎች የሚደረጉበት ቀን እና ሰዓት ታውቋል። ስለዚህም እነዚህ ተሰርዘው የነበሩ ጨዋታዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 1ኛ ዙር ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚከናወኑ የደረሰን መረጃ ያሳያል። በዚህም መሰረት መከላከያ ከ መቐለ ከተማ እሁድ የካቲት 11/2010ዓ.ም በ11:00 ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ከ ድሬዳዋ ከተማ ሰኞ የካቲት 12/2010ዓ.ም በ11:00 ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ ሀሙስ የካቲት 08/2010ዓ.ም በ8:00 እንዲሁም በጉጉት ተጠብቆ የነበረው የቅ/ጊዮርጊስ እና የደደቢት ጨዋታ ደግሞ እሁድ የካቲት 18/2010ዓ.ም በ11:00 ሰዓት የሚደረጉ እንደሚሆን ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን የውድድር እና ስነ ስርዓት ኮሚቴ የወጣው ፕሮግራም ያሳያል። ከላይ የተጠቀሱት አራቱም ጨዋታዎች በአ/አ ስታዲየም የሚከናወኑ ይሆናል።
በሌላ ዜና ድሬ ላይ ሰኞ(ጥር 21/2010ዓ.ም) ሊደረግ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ ወደ ቅዳሜ(ጥር 19/2010ዓ.ም) እንዲሁም እሁድ (ጥር 20/2010ዓ.ም) ሊደረግ የነበረው የደደቢት እና የጅማ አባጅፋር የአ/አ ስታዲየም ጨዋታ ወደ ረቡዕ (ጥር 23/2010ዓ.ም) የተቀየሩ ጨዋታዎች ሲሆኑ በማግስቱ ሀሙስ(ጥር 24/2010ዓ.ም) ደግሞ ቅ/ጊዮርጊስ ከ ድሬዳዋ ከተማ የሚያደርጉት የአንደኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ የሚከናወን ይሆናል።
ከ13ኛ ሳምንት ጀምሮ ያሉ ሙሉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ከዚህ እንደሚከተለው ይሆናሉ።

አስተያየት ይስጡ