መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዜና | ቅ/ ጊዮርጊስ ወደ አንደኛው ዙር በቀጥታ አለፈ።
ቅዱስ ጊዮርጊስአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግዜናዎች

ዜና | ቅ/ ጊዮርጊስ ወደ አንደኛው ዙር በቀጥታ አለፈ።

አጋራ
አጋራ

በ22ኛው የቶታል የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከደቡብ ሱዳኑ አል ሰላም ዋሁ ክለብ ጋር እንዲያደርግ የጨዋታ መርኃ ግብር ወጥቶለት የነበረው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚው የደቡብ ሱዳኑ አል ሰላም ዋኡ በጨዋታው ላይ መገኘት ባለመቻሉ ጨዋታውን ማድረግ ሳይችል ቀርቷል። ይህ የደቡብ ሱዳን ቡድን እስከ የጨዋታው ዕለት ጠዋት 3:00 ድረስ አ/አ እንደሚገባ አሳውቆ የነበረ ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት ለጨዋታው ሳይመጣ ቀርቷል። ቢሆንም ግን የካፍ ህግ በሚያዘው መሰረት ተጨዋቾቹ እና የዕለቱ ዳኞች ሜዳ በመገኘት ከክብር እንግዶች ጋር ትውውቅ አድርገው ህጉ እስከ ሚፈቅደው ደቂቃ ድረስ ሜዳ ውስጥ ቆይተው ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል። ይህንንም ተከትሎ ቅ/ጊዮርጊስ በቀጥታ ወደ አንደኛው ዙር እንዲያልፍ አስችሎታል። በአንደኛው ዙርም ከዩጋንዳው ኬሲሲኤ እና ከማዳጋስካሩ ስናፕስ ስፖርት አሸናፊ ጋር የሚጫወት ይሆናል። ሁለቱ ቡድኖች ማዳጋስካር ላይ ተጫውተው ባለሜዳው ስናፕስ ስፖርት 2-1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
የፎቶ ምንጭ: ኑራ ኢማም

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...