በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እየተወዳደረ የሚገኘው ሲዳማ ቡና እና ዋና አሰልጣኝ የነበረው አለማየሁ አባይነህ(አሌኮ) መለያየታቸው ተሰምቷል። ለሁለቱ አካላት ለመለያየት እንደ ዋና ምክንያት ሆኖ የቀረበው አሰልጣኙ ከአንዳንድ ተጫዋቾች ጋር የነበረው አለመግባባት ሲሆን ይህ እንደዋና ምክንያት ቢጠቀስም ቡድኑ እያሳየ የሚገኘው ወጥ ያልሆነ አቋም እና የቡድኑ ማሽቆልቆል እንደሆነ የhatricksport.com ድረገፅ ምንጮች ተናግረዋል። በቀጣይ ቡድኑ ማንን አሰልጣኝ አድርጎ እንደሚሾም የታወቀ ነገር የለም።
ሲዳማ ቡና በዘንድሮው የውድድር አመት በሊጉ ካደረጋቸው 15ጨዋታዎች 4አሸንፎ በ6ቱ አቻ ወጥቶ በ5ቱ ተሸንፎ ማግኘት ከነበረበት 45ነጥቦች ከግማሽ በታች ማለትም 18ቱን ብቻ አሳክቶ ከወራጅ ቀጠናው በ5ነጥቦች ብቻ ርቆ 9ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።
አስተያየት ይስጡ