መነሻ ገጽ ቻን ዋልያዎቹ በቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከሱዳን አቻው ጋር አንድ አቻ ተለያዩ
ቻንየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከሱዳን አቻው ጋር አንድ አቻ ተለያዩ

አጋራ
አጋራ

​በሀገር ዉስጥ ተጫዋቾች ብቻ በሚከናወነዉ የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮን ሽፕ (ቻን) የኢትየጵያ ብሄራዊ ቡድን ተሳታፊ ለመሆን የመጨረሻ ጨዋታቸውን ከሱዳን ጋር የመጀመሪያው ጨዋታውን ዛረሰ በ10:00 ሰዓት  በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም አከናውኗል  በጨዋታው 1-1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡ በአስልጠኛ አሸናፊ በቀለ እሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው አጋማሽ በ4-4-2 አሰላለፍ ሲገባ ግብ ጠባቂ ጀማል ጣሰው ተከላካዮች => አብዱልከሪም መሐመድ  አስቻለው ታመነ  አንተነህ ተስፋዬ ደስታ ዮሀንስ  አማካዮች =>ሙሉአለም መስፍን  ታፈሰ ሰለሞን አዲስ ግደይ  ጋዲሳ መብራቴ  አጥቂዎች አብዱራህማን ሙባሪክ ፤ ጌታነህ ከበደ የገቡ ሲሆን በመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል፡፡ በአንፃሩ የሱዳን ብሔራዊ ቡድን በ መልሶ ማጥቃት ሙከራ ወደ ጎል መድረስ ችለዋል፡፡

በሁለተኛው አጋማሽ ሁለት የተጫዋቾች ቅያሪ ሲያደርጉ የቀኝ መስመር ተከላካዪን አብዱልከሪም መሀመድን በመሐል ክፍል ተከላካይ  አማካዩ ምንተስኖት አደነ ሲቀይሩ ሌላኛው ተጨዋች ታፈሰ ሰለሞንን በ ብሩክ ቃልቦሬ ቀይረው ወደ ሜዳ አስገብተዋል፡፡ የቡድኑን ቅርፅ በ3-5-2 ቀየረው ሁለተኛውን አጋማሽ ጀምረው ታይተዋል፡፡ በዚሁ የጨዋታ እንቅስቃሴ በሱዳን ብሔራዊ ቡድን ተደጋጋሚ የጎል ሙከራ ማድረግ ችለዋል፡፡
በ77 ደቂቃ የሰይፈዲን መክበኪክ  የዋልያ ተከላካዮች በማለፍ ወደ ሳጥን ይዞ በመግባት ሱዳንን መሪ ማድረግ ሲችል፡ ከ3ደቂቃዎች በኃላ ከጌታነህ ከበደ ተሰንጥቆ ያገኘውን ኳስ አብዱረህማን ሙባሪክ ዋልያዋችን አቻ ማድርግ ችሏል በዚሁ ጨዋታው ተጠናቋል፡፡
የአሰልጣኝ አስተያየት አሸናፊ በቀለ

ዛሬ ባጠቃላይ ጨዋታው ጥሩ አልነበረም፡፡የልጆቹ ከፍተኛ የልጆቹ  የማሸነፍ ፍላጎት ጨዋታውን እንዳናሸንፍ አድርጎናል፡፡

የመልቀቂያ ደብዳቤ ስለማስገባታቸው ተጠይቀው ?
መልቀቂያውን አውነት ነው አስገብቻለሁ ::

-መልቀቂያ የማስገባትህ ምክኒያት ?ከፌዴረሽኑ ጋር  ያለህ ቅሬታህ ምንድነው?

 ባሁን ሰዓት ምክኒያቱን ለመናገር ፍቃደኛ አይደለሁም፡፡ በቀጣይ ግዚያት እናገራለሁ ሲሉ አጠቃለዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ከሜሲ ጋር በአንድ ሜዳ የደመቀው የሜጀር ሊግ ሶከሩ ኮከብ ማረን ሀይለስላሴ

የማረን ሁለቱ ታናናሽ ወንድሞቹም እግር ኳስን ተጫውተዋል አሁን ላይስ ምን ላይ ናቸው።...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የእናቱን ሀገር መለያ የመልበስ ፍላጎት ያለው የግራ መስመር አጥቂ

ለአሜሪካ ከሀያ አመት በታች ብሔራዊ ቡድን የተጫወተው እና በዴንማርክ የሚገኘው ተጫዋች። እናቱ...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

“ኢትዮጵያን ባገለግል እጅግ ደስ ይለኛል” ወጣቱ ተጫዋች ጆሲሳ ስምዖን

በጀርመኑ ኮሎኝ የሚገኘው እና በቀጣዩ ክረምት ወደ ዋናው ቡድን የሚያድገው ወጣቱ የግራ...