ወላይታ ዲቻ የመጨረሻ ልምምዱን ዛሬ ረፋድ 4:00 ላይ በሐዋሳ አለማቀፍ እስቴድየም ሰርተዋል።ዚማሞቶ አሸንፈው የመጡት ወላይታ ዲቻዎች ነገ በሐዋሳ አለማቀፍ እስቴድየም የግብፁን ዛማሊክን ለሚያስተናግድበት ጨዋታ ጠንካራ ልምምድ ሲያረጉ ከቆዮ በላ ዛሬ ረፋድ ላይ ማላቀቂያ ሰርተዋል ።ለወትሮው ከሚታወቁበት መከላከል ላይ መሰረት ያደረግው አጨዋወት ለየት ባለ መልኩ አጥቅተው ለመጫወት እዳሰቡ የሚሳይ ልምምድ ተመልክተናል።በነገው ጨዋታ ወላይታ ድቻ ዳግም በቀለን እማያገኝ ሲሆን እሱን ተክቶ አምረላ ደልታታ እንደሚሰለፍ አሰልጣኝ ዘነበ ፍስሀ ገልፀዋል።
ተጋጣሚው ዛማሊክ ዛሬ 10:00 ላይ የመጨረሻ ልምምድዳቸውን ሰርተዋል። ዛማሌክ በትናንትናው እለት ሀዋሳ የገቡ ሲሆን ማረፊያቸውን አሮሪ ሆቴል ያደረጉ ሲሆን ዛሬ 10 ሰዓት ላይ የሁለተኛ ቀን ልምምዳቸውን አከናውነዋል።
በልምምዳቸው ወቅት አጥቅተው በመጫወት ጨዋታውን ለማሸነፍ እሚችሉበትን ትሬኒንግ ሲተገብሩ ተስተውሏል።
ዛማሊኮች ከግብፅ 20 ተጫዋቾችን ይዞ ሲመጣ ሁሉም ተጫዋቾች ለጨዋታው ዝግጁ መሆናቸው ተገልፆል።
የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ነገ በ10:00 ሰዓት በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ሲከናወን የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዝን እንዲሁም የግብፁ ቴሌቪዥን ጨዋታውን በቀጥታ እንደሚያስተላለፍ ይጠበቃል።

አስተያየት ይስጡ