መነሻ ገጽ ኢትዮጵያ ቡና ኢትዮጵያ ቡና እና ጋቶች ፓኖም ሳይስማሙ ቀሩ።ቀጣይ ማረፊያው የት ይሆናል?
ኢትዮጵያ ቡናየዝውውር ዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና እና ጋቶች ፓኖም ሳይስማሙ ቀሩ።ቀጣይ ማረፊያው የት ይሆናል?

አጋራ
አጋራ

የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና እና የአንዚ ማካቻካላ ተጫዋች የነበረው ጋቶች ፓኖም ለኢትዮጵያ ቡና ጋር ዳግመኛ የማገልገሉ ነገር ተጨናግፏል። 

የኢትዮጵያ ቡና የፌስቡክ ገፅ እንዳስነበበው “ድርድሩ ሊሳካ ያልቻለው ጋቶች ለክለቡ ባቀረበው የተጋነነ የክፍያ ጥያቄ አማካኝነት ነው።ጋቶች በየወሩ የተጣራ 250.000ብር የጡረታ ወይም የስራ ግብርን ሲጨምር 37800 ብር በድምሩ ለስድስት ወራት 1.5 ሚሊዮን ብር ጠይቋል።” በማለት ጠቅሶ ” የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብም ካለው አቅም አንጻር ለጋቶች ፓኖም በወር ታክስን ጨምሮ ለአንድ አመት 130,000 ብር እንዲሁም ለሁለት አመት በወር 150,000 ብር ለመክፈል እና ጋቶች የውጭ እድል ባገኘ ጊዜ ክለቡ በዝውውር ሊያገኝ የሚገባውን ጥቅም በመተውና እና ከተጨዋቹ የሚያገኛቸው ግልጋሎቶች ለጋቶች ክብር ሲባል ለመተው ሀሳብ ቢያቀርብም ተጨዋቹ በሀሳቡ ባለመስማማትና ከሌሎች ክለቦች የተሻለ ክፍያ እንዳገኘ በመግለጡና ለቡና ለመጫወት ባለመፍቀዱ ድርድሩ እንዲቋረጥ ተስማምተዋል።

ኢትዮጵያ ቡና ከዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ የተገደደው ክለቡ ካለው የመክፈል አቅም ብቻም ሳይሆን ለአንድ ተጨዋች የተጋነነ ክፍያ ለመፈጸም የማይፈቅደው ብዙም የብቃትና የችሎታ ልዩነቶች በሌለበት ሊግ ውስጥ የቡድኑን ሌሎች ተጨዋቾች የመጫወት ፍላጎት ላይ ተጽእኖ ላለማድረስ፣ በቡድን ብቃት ላይ የተለየ ተፅዕኖና በቀጣይ የተጨዋቾች ዝውውር ላይ የተለየ ጫና ላለመፍጠር ካለው አላማ አንጻርም ጭምር ነው።” በማለት አክሏል።
ጋቶች በኢትዮጵያ ቡና ከወጣትነቱ ጀምሮ የተጫወተ ሲሆን ወደ ሩሲያው ክለብ አንዚ ማካቻካላ እስከተዛወረበት እለት ድረስ ለቀድሞ ቡድኑ ከፍተኛ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር። በአንዚ በቋሚነት በቂ የመሰለፍ እድል ያላገኘው ጋቶች ከክለቡ ጋር ያለውን ውል በስምምነት አፍርሶ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ዘመን ጀምሮ መጫወት የጀመረ ሲሆን አሁንም እያገለገለ ይገኛል። ከሩሲያ ከተመለሰ በኋላም ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ልምምድ እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል።

የጋቶች ቀጣይ ማረፊያ የት ይሆናል ለሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ እየተነሳ ሲሆን ከሀገር ውስጥ ወላይታ ድቻ እና መቐለ ከተማ ግንባር ቀደም ፈላጊዎቹ ሆነው ቀርበዋል። ከሀገር ውጪ ደግሞ ስማቸው ያለተጠቀሰ ክለቦች የልጁ ፈላጊ ሆነው ብቅ ብለዋል። የጋቶች ቀጣይ ማረፊያ በቅርቡ የሚታወቅ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

  • ተጨዋቾች ከሚጫወቱበት ቡድን ጋር ላለመቀጠል ሲፈልጉ የሚያቀርቡት ክፍያ የተጋነነ መሆን አዲስ ነገር አይደለም ፡፡ የክለብ አመራሮች ፣ እግር ኳሱን በበላይነት የሚመራው የእግር ኳስ ፌደሬሽን ፤ የክለቡ ባለቤት የሆኑት የመንግስትና የልማት ድርጅቶችና የሚዲያ አካላት በተጨዋቾችና አሰልጣኞች አመላመል እና ዝውውር ጉዳይ ላይ የሚጠየቀውን ክፍያ በተመለከተ ቀርበው ካልተነጋገሩ ከአቅም አኳያ በርካታ ክለቦች የመፍረስ ዕጣ እንደሚያጋጥማቸው ጥርጥር የለውም ፡፡ በተግባርም የታየ ጉዳይ ነው ፡፡ በአለምና በአፍሪካ የእግር ኳስ ደረጃችን ምን ላይ ነው ያለው ? በሀገራችን እየተካሄዱ ያሉት ውድድሮች ተመልካችን የሚያዝናኑና ለወደፊት ለሚገነባው ብሄራዊ ብድን የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚመጥን ነው ? ድርጅቶች ከገቢ አኳያ ተጠቃሚ ናቸው ወይ ? የሚለው መታሰብ ያለበት ጉዳይ ይመስለኛል ፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
አርሲ ነገሌዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ነገሌ አርሲ በነፃ ዝውውር ናይጄሪያዊ አጥቂ አግኝቷል

በኢራቅ ሊግ ቆይታ የነበረው አጥቂ ነገሌ አርሲን ይቀላቀላል። ኪቲካ ጀማን በዝውውሩ የመዝጊያ...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

መቐለ 70 እንደርታ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ

መቐለ 70 እንደርታ ክለብ የሌለውን አጥቂ ወደ ክለቡ አምጥቷል። በአሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም...

መቐለ 70 እንደርታኢትዮጵያ መድህንዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ጋናዊው ተጫዋች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ለመድን ፈረመ

ኢትዮጵያ መድን የአጋማሹን አራተኛውን ፈራሚ አግኝቷል። በአሰልጣኝ ገብረመድኅን ሐይሌ የሚመሩት የወቅቱ የሊጉ...

ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ወልዋሎ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ

ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ አራተኛውን የአጋማሹን አዲስ ፈራሚ በእጃቸው አስገብተዋል። በአሰልጣኝ ግርማ ታደሠ...