በክረምቱ የተጨዋቾች ዝውውር ሁለት የመሐል ተጨዋቾች ያጡት ሻምፒዮኖቹ መቐለ 70 አንደርታዎች የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋች አዲስ ህንፃን ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል።
ባሳለፈነው የውድድር ዓመት ከአዳማ ከተማ ጋር ያሳለፈው አዲስ ህንፃ ሃይደር ሸረፋና ጋብርኤል መሃመድን ያጣውን የመቐለ 70 አንደርታ የመሐል ክፍል ሊያጠንክር አንደሚችል ይገመታል።

ከዚህ በፊት ለኢትዮጵያ ባንኮች፣ደደቢት፣አልሃሊ ሸንዲ(ሱዳን)፣አዳማ ከተማ መጫወት የቻለው አዲስ ሃንፃ መቐለ ላይ የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን በማካሄድ ላይ ያለውን የመቐለ 70 አንደርታን ስብስብ ዛሬ ጠዋት ተቀላቅሎ ከቡድኑ ጋር ልምምድ መስራት ችልዋል።
አስተያየት ይስጡ