መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና አስተያየት | ስሑል ሽረ 0-0 ሀዲያ ሆሳዕና
ሀዲያ ሆሳዕናስሁል ሽረዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አስተያየት | ስሑል ሽረ 0-0 ሀዲያ ሆሳዕና

አጋራ
አጋራ

“የዛሬው ጨዋታ ደካማ እንቅስቃሴ ያሳየንበት ነበር”

ምክትል አሰልጣኝ መብራህቶም ፍስሀ(ስሑል ሽረ)

“ክለባችን መሻሻል ይፈልጋል ዝምብለህ ስር ነቀል ሳይሆን ጥገና ነው ሚያስፈልገው”

ፀጋይ ኪዳነማርያም (ሀድያ ሆሳእና)


 

ምክትል አሰልጣኝ መብራህቶም ፍስሀ

ስለ ጨዋታው

“የዛሬው ጨዋታ ደካማ እንቅስቃሴ ያሳየንበት ነበር ምክንያቱም የኛ ተጨዋቾች ሙለ ዘጠና ደቂቃ ጫና ውስጥ ነበሩ፣ከነ ጉዳታቸው የገቡ ነበሩ፣በቅጣት እና በጉዳት ያጣናቸው ተጨዋቾች ነበሩ።በረኛችን ሳናስበው በጉዳት መቀየራችን ቅያሬዎቻችንን አበላሽቶብናል።ሀድያዎች ጥሩ ተከላክለዋል፤ታክቲካል ጥሩ ስለነበሩ እንደ ሌላው ጊዜ ብዙ እድሎችን መፍጠር አልቻልንም።ተከላክለው ለመውጣት ሚመጡትን ቡድኖች እንዴት ማስከፈት አንዳለብን ለቀጣይ ተዘጋጅተን እንመጣለን።ዛሬ ሁለት ነጥቦችን አጥተናል እነዚህን ነጥቦችን ለማካካስ ቀጣይ ባህርዳርን ለማሸነፍ ነው ምንዘጋጀው።

ፀጋይ ኪዳነማርያም(ሀድያ ሆሳዕና)

 

“እንደምታቁት ቡድኑን ከተቀላቀልኩኝ አንድ ሳምንት ነው የሆነኝ ልጆቹን ውድድር ላይ ነው ያገኘሁዋቸው አጋጣሚ ሆኖም የአሰልጣኞች ቡድን የለኝም።እዚ የነበሩት ስለለቀቁ ብቻዬን ነው ያለሁት እናም አንዳንድ ማግኘት ምፈልጋቸው መረጃዎች ማግኘት አልቻልኩም።ሆኖም ግን ፈታኝ ጊዜ ላይ ነው ቡድኑን የያዝኩት ይህንን ፈተና ለማለፍ ነው ሀላፍነት ይዤ የገባሁት።”

ቡድኑን ከወራጅነት ለማትረፍ እየተደረገ ስላለው ዝግጅት

“ቀሪውን አንድ ጨዋታ በስነልቦና ደረጃ ነው እያዘጋጀን ያለነው ተስፋ እንዳይቆርጡ ሁሉንም ጨዋታዎች እንደ ጥሎ ማለፍ እንዲያይዋቸው እያደረግን ነው።ክለባችን መሻሻል ይፈልጋል ዝምብለህ ስር ነቀል ሳይሆን ጥገና ነው ሚያስፈልገው።ሚታዩ ክፍተቶች አሉ በሁሉም ቦታዎች እነሱን ለመድፈን ጠንከር ያሉ ሊጉን ሚያቁ ተጨዋቾች ያስፈልጉናል።ልምድ ያላቸው ተጨዋቾች ያስፈልጉናል እንደምታዩዋቸው የኛ ተጨዋቾች ብዙ ልምድ የላቸውም ስለዚ በነዚህ ክፍተቶች ላይ እየሰራሁኝ ነው።”

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...