መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ ነፃነት ገብረመድህን ምዓም አናብስቶቹን በይፋ ተቀላቅሏል
መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ነፃነት ገብረመድህን ምዓም አናብስቶቹን በይፋ ተቀላቅሏል

አጋራ
አጋራ

 

የነባር ተጨዋቾቻቸውን ውል በማራዘም በይፋ ወደ ዝውውር መስኮቱ የተቀላቀሉት መቐለ 70 እንደርታዎች ነፃነት ገብረመድህንን የክረምቱ የመጀመርያ ፈራሚያቸው አድርገውታል።

ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከስሑል ሽረ ጋር የተሳካ ጊዜ ማሳለፍ የቻለው ወጣቱ የተከላካይ አማካይ ከጋብርኤል አህመድ(ጅብሪል) መልቀቅ በኃላ ሁነኛ ተተኪ አጥተው ለነበሩት መቐለዎች ጥሩ መፍትሄ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።ኳሶች ማጨናገፍና ለተከላካይ ክፍል ሽፋን መስጠት ላይ የተካነው ነፃነት የትውልድ ከተማው ክለብ ስሑል ሽረን ከበርካታ ዓመታት ቆይታ በኃላ ሊሰናበት ችሏል።

በተያያዘ ዜና መቐለ 70 እንደርታዎች የነባር ተጨዋቾቻቸውን ውል የማራዘም ስራቸውን በማስቀጠል የስዩም ተስፋዬ፣ዮናስ ገረመው እና አሚን ነስሩን ውል አራዝመዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...