በወቅቱ የተጨዋቾች ዝውውር ላይ መሳተፋቸውን የጀመሩት መቐለ 70 እንደርታዎች በረከት አማረን ከኢትዮጵያ ቡና አስፈርመዋል።
ከኢኳቶሪያል ጊናዊው ግብ ጠባቂ ፊሊፕ ኦቮኖ ጋር የተለያዩት መቐለዎች ባሳለፍነው ዓመት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ያሳለፈው በረከት አማረን ማስፈረም ችለዋል።የቀድሞ የወልዋሎ፣አማራ ውሃስራ ግብ ጠባቂ በረከት የቀዋሚ ተሰላፊነትን ለማግኘት ከሶፈንያስ ሰይፈ ጋር ከፍተኛ ፋክክር ሚጠብቀው ይሆናል።