በትግራይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ትግራይ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ና ሽቶ ሚድያ ኮሚዩኒኬሽን አስተባባሪነት ተዘጋጅቶ ላለፋት 9 ቀናት በትግራይ ስታድየም ሲካሄድ የነበረው ትግራይ ዋንጫ ነገ በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ፍፃሜውን ያገኛል።
7 ክለቦችን በሁለት ምድብ በመክፍል የምድብ ጨዋታዎችን ያከናወነው ውድድሩ፤በውድድሩ ህገ መተዳደርያ ደንብ መሰረት ከየምድባቸው አንደኛ የወጡትን ተጋባዦቹ ወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና ለፍፃሜ ሲያገናኝ ከየምድባቸው ሁለተኛ ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁትን አክሱም ከተማ ና ሰሎዳ ዓድዋን ለደረጃ አገናኝትዋል።
ነገ 6:30 ሚጀምረው የመዝጊያ ስነ-ስርዓት የመቐለ 70 እንደርታ ደጋፊዎች በሁለት ተከፍለው በሚያደርጉት የወዳጅነት ጨዋታ ጅማሮውን በማድረግ የደረጃ ና የዋንጫ ጨዋታዎችን በማስከተል ፍፃሜውን ሚያገኝ ይሆናል።በየጨዋታው ኮከብ ተጨዋቾችን ስታር ታይምስ ዲኮደሮችን እየሸለመ ሚገኘው ትግራይ ዋንጫ፤የውድድሩ ኮከብ ተጨዋች፣እና ኮከብ አሰልጣኝ እና ሌሎች ሽልማቶችን አካቶ ጨምሮ ነገ በደማቅ ስነ ስርአት ፍፃሜውን ያገኛል።
የደረጃ ጨዋታ
7:30 | አክሱም ከተማ ከ ሰሎዳ ዓድዋ
የዋንጫ ጨዋታ
9:30 | ወላይታ ድቻ ከ ሲዳማ ቡና
አስተያየት ይስጡ