መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና ተክለማርያም ሻንቆ የገብረመድህን ሃይሌ ስብስብን ለመቀላቀል ተስማምቷል !
ሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

ተክለማርያም ሻንቆ የገብረመድህን ሃይሌ ስብስብን ለመቀላቀል ተስማምቷል !

አጋራ
አጋራ

ለኢትዮዽያ ቡና ተጠባባቂ  ለዋሊያዎቹ ዋነኛ ተመራጭ ግብ ጠባቂ የነበረው ተክለ ማርያም ሻንቆ/ጎሜዝ/ ከነሀሴ 1/2013 ጀምሮ የሲዳማ ቡና ለመሆን ተስማምቷል።

ግብ ጠባቂው  በኢትዮዽያ ቡና  እስከ ሀምሌ 30/2013 ድረስ ውል ያለው በመሆኑ ፌዴሬሽን ተገኝቶ ለሲዳማ ቡና ፊርማውን አኑሮ ህጋዊ የሚሆነው ከነሀሴ 1/2013 ጀምሮ ይሆናል።

ግብ ጠባቂው በጥር ወር ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ቋሚ ተሰላፊ ለመሆን  በክለብ ደረጃ ቋሚ መሆንና ከሌሎች ግብ ጠባቂዎች ጋር መፎካከር የግድ በመሆኑ ለኢትዮዸያ ቡና ያቀረበው የቋሚ ተሰላፊነት ማረጋገጫ ተቀባይነት ባለማግኘቱ  ሊለቅ መቻሉ ታውቋል።

የሲዳማ ቡናው አሰልጣኝ ገብረ መድህን ሃይሌ ለጎሜዝ የቋሚ ተሰላፊ  የመሆን ዋስትና መስጠቱና ተደጋጋሚ የማስፈረም ጥረቱ ተሳክቶ ለ2 አመት ለሲዳማ ቡና ለመጫወት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

በሁለቱ ወገኖች ስምምነት መሰረት ተክለማርያም 3.5 ሚሊዮን  ብር ለ2 አመት እንዲከፈለው የተስማማ ሲሆን 2.5 ሚሊየን ብሩ በቼክ መቀበሉ ታውቋል። ቀሪው 1 ሚሊዮን ብር ደግሞ በውል ዘመኑ መሰረት ለ24 ወር የሚከፋፈልና በደሞዝ መልክ የሚወስደው መሆኑ ታውቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...