መነሻ ገጽ አፍሪካ ባምላክ ተሰማ አርብ የሚካሄደውን የካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ጨዋታን እንዲመሩ ተመርጠዋል።
አፍሪካአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግዜናዎች

ባምላክ ተሰማ አርብ የሚካሄደውን የካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ጨዋታን እንዲመሩ ተመርጠዋል።

አጋራ
አጋራ

በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ጨዋታ የፊታችን አርብ ካይሮ ላይ ሚካሄደው የዛማሌክ እና የዛምቢያው ዜስኮ ዩናይትድን ጨዋታ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ ሊዳኙት መመረጣቸውን የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን(ካፍ) አስታውቋል።

ምድቡን ሀያሎቹ ቲፒ ማዜምቤ በ7 ነጥቦች ሲመሩ የግብፁ ሀያል ክለብ ዛማሌክ በ4 ነጥብ ይከተላል። ዛማሌክን የሚገጥሙት ዜስኮዎች በሁለት ነጥብ የምድቡ ግርጌ ላይ ተቀምጠዋል።

በምድቡ ሶስተኛ ጨዋታ ዛምቢያ ላይ አቻ የተለያዩት ሁለቱም ቡድኖች ነገ የሚያካሂዱትን ጨዋታ በ39 ዓመቱ ባምላክ ተሰማ መሪነት ግብፅ ካይሮ ስታድየም ላይ ይካሄዳል።

በዛማሌክ ና አርኤስ ቤርካን መሀከል የተካሄደውን የአምናው የካፍ ኮንፌዴሬሽን የፍፃሜ ጨዋታን መዳኘት የቻሉት ባምላክ ተሰማ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአፍሪካ መድረክ ላይ ያላቸው ተቀባይነት እየጨመረ ሄዷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...