በአለም ዋንጫ ማጣሪያ ከኢትዮጵያ ጋር የተደለደለችው ዚምባብዌ አዲስ አሰልጣኝ ቀጥራለች
ዚምባብዌ ክሮሺያዊ አሰልጣኝ በይፋ ቀጥራለች።
በአለም ዋንጫ ማጣሪ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጋር የተደለደለችው ዚምባብዌ ክሮሺያዊው አሰልጣኝ ዝድራቮክ ሎጋሩስኪ በሁለት አመት ኮንትራት በይፋ መቅጠሯን ፌደሬሽኑ አሳውቋል። በአለም ዋንጫ ምንም ተሳትፎ የሌላት ብሄራዊ ቡድኗ አዲሱ አሰልጣኝ ይህን የቤት ስራ መወጣት ይጠበቅባቸዋል። አሰልጣኙ ከዚህ ቀደም የሱዳን ብሄራዊ ቡድንን ጨምሮ ትልልቅ የሚባሉ የጋና፣ኬንያ፣አንጎላ እና ታንዛኒያ ክለቦች ማሰልጠን ችለዋል። አሳቸውን የሚረዱ ሌሎች አራት ረዳት አሰልጣኞችም ተመድበዋል።
አስተያየት ይስጡ