የካፍ የ2018/19 የቻምፒዮንስ ሊግ ድልድል ትላንትና ይፋ ሆንዋል በዚህም መሰረት የ2010 የኢትዮጰያ ፕሪሚየርሊግ አሸናፊ የሆነው ጅማ አባጅፋር የመጀመርያ ዙር የጥሎ ማለፍ ተጋጣሚውን አውቋል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አሸናፊው የሆነው ጅማ አባጅፋር ከ ጅቡቲው አሸናፊ የሆነው ኤኤስ ጅቡቲ ቴሌኮሞ ጋር ተመድብዋል። ይህም ጨዋታ በካፍ ፕሮግራም መሰረት የመጀመርያው ዙር ህዳር 18 ወይም 19 ሲደረግ የመለሱ ጨዋታ በሳምንቱ ህዳር 25/26 አዲስ አበባ ላይ የሚጫወቱ ይሆናል።
የዚሁ ጨዋታ አሸናፊ በሁለተኛው ዙር የግብፁን አልሀሊ የሚገጥም ይሆናል ጅማ አባጅፋር የጅማ ዩኒቨርሲቲ ስቴድየም ባለመጠናቀቁ ጨዋታው አዲስ አበባ ስቴድየምን በማስመዝገቡ አዲስ አበባ ላይ የሚጫወት ይሆናል
አስተያየት ይስጡ