መነሻ ገጽ ስሁል ሽረ ስሑል ሽረ ሁለት ተጨዋቾችን አስፈረመ
ስሁል ሽረዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ስሑል ሽረ ሁለት ተጨዋቾችን አስፈረመ

አጋራ
አጋራ

 

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ የውድድር ዓመታቸውን ለማሳለፍ እየተዘጋጁ ሚገኙት ስሁል ሽረ የሃይለአብ ሃይለስላሰና ብሩክ ተሾመ ዝውውርን አጠናቀዋል።

ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከሻምፒዮኖቹ ጋር የአንድ ዓመት ቆይታ ያደረገው የትራንስ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ቡድን ውጤት የሆነው የመሃል ሜዳ ተጨዋቹ ሃይለአብ የሳምሶን አየለን ስብስብ ተቀላቅሏል።መሀል ላይ የፈጣሪ ተጨዋች እጥረት የነበራቸው ስሑል ሽረ ሃይለአብን ማስፈረማቸው በመጠኑ ችግራቸውን ሊፈታላቸው አንደሚችል ይገመታል።የቀድሞው ዋልታ ፖሊስ፣መቐለ 70 አንደርታ፣ወልዋሎና ደደቢት ተጨዋች ሃይለአብ ከስሑል ሽረ ጋር ለቀጣይ ሁለት ዓመት ቆይታ ይኖረዋል።

ሌላ ስሑል ሽረን የተቀላቀለ ተጨዋች ብሩክ ሓዱሽ ነው።ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከሰበታ ከተማ ጋር የከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ ሻምፒዮን የሆነው ብሩክ በሁለት ዓመት ውል የቀድሞ ክለቡን ስሑል ሽረን ተቀላቅሏል።ከዚህ ቀደም ለፋሲል ከነማ፣ሰበታ ከተማ እና ስሑል ሽረ የተጫወተው ብሩክ ሓዱሽ የስሑል ሽረ የአጥቂ ክፍል ያጠናክራል ተብሎ ይገመታል።

በተጨማሪ ስሑል ሽረ የሥስት ነባር ተጨዋቾቻቸው ክፍሎም ገብረሂወት ፣ሰይድ ሀሰን እና ሸዊት ዮውሃንስ ውል ሲያራዝሙ ከዲሜጥሮስ ወልደስላሴ ና ብሩክ ተሾመ ጋር ተለያይተዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...