መነሻ ገጽ ስሁል ሽረ ስሁል ሽረ ከሁለት ተጨዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይተዋል
ስሁል ሽረዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ስሁል ሽረ ከሁለት ተጨዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይተዋል

አጋራ
አጋራ

 

በወቅቱ የተጨዋቾች ዝውውር ላይ 9 አዳዲስ ተጨዋቾችን ያስፈረሙት ስሑል ሽረዎች ከብሩክ ተሾመና ዲሜጥሮስ ወልደስላሴ ጋር በስምምነት ተለያይተዋል።

ባሳለፍነው የውድድር ዓመት አጋማሽ ስሁል ሽረን በመቀላቀል ቡድኑ ከወራጅነት እንዲተርፍ ያገዘው ሁለገብ ተጨዋቹ ብሩክ ተሾመ ከግማሽ ውድድር ዓመት ቆይታ በኃላ በስምምነት ከክለቡ ጋር ተለያይትዋል።የቀድሞው የጅማ አባጅፋር፣ደደቢት፣ተጨዋች ብሩክ በግማሽ ዓመት የስሁል ሽረ ቆይታው የቀኝ መስመር ተከላካይ፣የመሀል ሜዳ አማካይ ና የመሀል ተከላካይ ሆኖ መጫወት ችሏል።ሌላኛው ከስሁል ሽረ ጋር የተለያየው ተጨዋች ዲሜጥሮስ ወልደስላሴ ነው፤በ2011 ከአዲስ አበባ ከተማ የፈረመው ዲሜጥሮስ በአንድ ዓመት ቆይታው ስሁል ሽረን በአምበልነት መርቷል።የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ፣ሀረር ቢራና አዳማ ከተማ ተከላካይ ዲሜጥሮስ በክረምቱ ከስሁል ሽረ ጋር የተለያየ 10ኛው ተጨዋች ሆኗል።

በተያያዘ ዜና ትላንትና የሥስት ነባር ተጨዋቾቹ ውል ያራዘመው ስሁል ሽረ ከሥስቱ ተጨዋቾች በተጨማሪ የነፃነት ገብረመድህን፣ጌታቸው ተስፋይ፣ክብሮም ብርሃነ፣ዋልታ ዓንደይ፣ተኽላይ በርሀን ውል ሲያራዝም በቀጣይ ቀናትም 4 ተጨዋቾችን ከሁለተኛ ቡድኑ ሚያሳድግ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...