መነሻ ገጽ ሰበር ዜና ሰበር ዜና | በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የፊፋ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ ለፌዴሬሽኑ ተላከ አስመራጭ ኮሚቴው እንዲፈርስ ዕጩ ተወዳዳሪዎችም እንደ አዲስ እንዲወዳደሩ ወሰነ
ሰበር ዜናዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

ሰበር ዜና | በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የፊፋ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ ለፌዴሬሽኑ ተላከ አስመራጭ ኮሚቴው እንዲፈርስ ዕጩ ተወዳዳሪዎችም እንደ አዲስ እንዲወዳደሩ ወሰነ

አጋራ
አጋራ

ለወራቶች ሲያወዛግብና መፍትሔ አጥቶ የቆየው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፕሬዝዳንት እና የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫ በፊፋ የመጨረሻ ውሳኔ ያገኘ ይመስላል።
ፊፋ ለበርካታ ወራቶች የእግር ኳሱን መንደር ሰላም ነጥቆ ለቆየውና አልቋጭ ብሎ ላስቸገረው ውዝግብ መፍትሄ ይሆናል ብሎ ያመነበትን ውሳኔ የፊፋ አጣሪ ኮሚቴ ይፋ አድርጓል።
ትናንት ምሽት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ደረሰ እንደተባለውና ሀትሪክ ከታማኝ ምንጮቿ እንዳገኘችው መረጃ መሠረት የፊፋ አጣሪ ኮሚቴ ከሁለት ሳምንት በፊት ያደረገውን ማጣራት ተከትሎ የመጨረሻ ያለውን ውሳኔ በመወሰን ለፌዴሬሽኑ በደብዳቤ አሳውቋል።
ሀትሪክ ጋዜጣና ድረ ገፅ እንዳገኙት መረጃ ከሆነ ፊፋ ትናንት ምሽት በላከው ደብዳቤና ውሳኔ መሠረት ቀደም ሲል በአስመራጭነት ሲሰራ የነበረው ኮሚቴ ሙሉ በሙሉ እንዲፈርስና አዲስ አስመራጭ ኮሚቴ እንዲቋቋም ለፕሬዚዳንትነትና ለስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ሲወዳደሩ የነበረው በሙሉ እንዲሰረዝና እንደ አዲስ ዕጩዎች እንዲቀርቡ ፌዴሬሽኑም አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት የፊፋን የምርጫ ህግ እንዲያፀድቅና በህጉ መሠረትና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ምርጫውን እንዲያከናውን የፊፋ አጣሪ ኮሚቴ ጠንከር ያለ ውሳኔ አስተላልፏል።
ይህ የፊፋ ውሳኔ ያልተጠበቀና ብዙዎችን ያስደነገጠ ሲሆን በተለይ ለስልጣን ሲቋምጡ የነበሩና ለውዝግቡ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑ ግለሰቦች በውሳኔው ክፉኛ መደናገጣቸው የተሰማ ሲሆን በፊፋ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ መሠረት ክልሎች አዳዲስ ዕጩዎችን ሲመርጡ አሁን ከሰሩት ስህተት በመታረም በጥንቃቄ መምረጥ እንዳለባቸው ነው አስተያየት ሠጪዎች የሚናገሩት።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...