መነሻ ገጽ ሪፖርት ሪፖርት | ወልዋሎ ላለመውረድ የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሎበታል
ሪፖርትወልዋሎየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግደደቢት

ሪፖርት | ወልዋሎ ላለመውረድ የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሎበታል

አጋራ
አጋራ

በ 26ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሜየርሊግ ዓዲግራት ላይ የተደረገው የወልዋሎ እና ደደቢት ጨዋታ በወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ኣሸናፊነት ተጠናቅዋል።
ወልድያን ካሸነፈው ቡድን ማናዬ ፋንቱን በ ጋናዊው ኣብዱራህማን ፋሱይኒ ቀይረው ገብተዋል።

በኣሰልጣኛቸው ንጉሴ ደስታ ድንገተኛ ሞት ምክንያት የ 25ተኛ ሳምንት ጨዋታቸውን ያልተጫወቱት ደደቢቶች ቡናን ከገጠመው ቡድን እንዶህ ኩዌኬን በቅጣት በያኣብስራ ተስፋዬ እንዲሁም በጉዳት ምክንያት ከቡድኑ ርቆ የቆየው ግብ ጠባቂው ክሌመንት በ ታሪኬ ጌትነት ቀይረው ገብተዋል።

በዝናብ ታጅቦ የጀመረው የመጀመርያው አጋማሽ በሁለቱም ቡድን በኩል ብዙየጎል ሙከራ የታየበት ነበር።መሃል ሜዳ ላይ ሲደረጉ የነበሩ ቅብብሎች በሜዳው መጨቅየት ምክንያት ለመጫወት ሲያስቸግራቸው ነበር።

መሃል ሜዳ ላይ የተሻለ የጨዋታ ብልጫ መውሰድ የቻሉት ወልዋሎዎች የግብ ሙከራ በማድረግም ቀዳሚ ነበሩ በተለይም ራችሞንድ ኦዶንጎ እና ፕሪንስ ያደረግዋቸው ሙከራዎች ተጠቃሽ ናቸው።

ደደቢትም ከተከላካይ ክፍሉ በሚጣሉ ረጃጅም ኳሶች የወልዋሎን ተከላካይ ክፍል ሲፈትኑ ነበር በተለይም ኣቤል ያለው ያመከናቸው ኳሶች ኣስቆጪ ነበሩ።

ባለሜዳዎቹ በ28ተኛው ደቂቃ ያገኙትን ማኣዘን ምት በኣጭሩ በማስጀመር ከግራ መስመር ኣለምነህ ያሻማውን ኳስ በረከት ተሰማ በግንባሩ በመግጨት ወልዋሎን መሪ ማድረግ ችሏል።ከግቧ መቆጠር በኋላ ደደቢቶች ኣቻ ለመሆን ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካላቸው ቀርቷል።

 

ሁለተኛው ኣጋማሽ ሹክቻ የበዛበት ብዙ ሙከራ ያልታየበት ነበር።የ ሁለተኛው ኣጋማሽ ሚጠቀስ ሙከራ ዋለልኝ ገብሬ በፍፁም ቅጣት ምት ሳጥን ጠርዝ ላይ ያገኘውን ኳስ በባናና ምት ጠምዝዞ ቢመታውም ክሌመንት በሚገርም ብቃት ኣድኖበታል።

ከ 60ኛው ደቂቃ በኃላ ደደቢት ተጭነው ቢጫወቱም የኣቻነት ግብ ማግኘት ኣልቻሉም።ይባስ ብሎ ኣማካይ ተጫዋቻቸው ኣስራት በሁለት ቢጫ በቀይ ኣጥተዋል።ጨዋታውም ሌላ ጎል ሳያስተናግድ በወልዋሎ ዩኒቨርስቲ ዓዲግራት ኣሸናፊነት ተጠናቋል።

ደረጃ ሰንጠረዥ 

 
[team_standings id=”6559″ title=”” number=”16″ columns=”p,gd,pts” show_team_logo=”1″ show_full_table_link=”1″ align=”right”]

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...