መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ ሪፖርት | ቅ/ጊዮርጊስ አሁንም ከሜዳው ውጪ ድል ማስመዝገብ አልቻለም።
ሀዋሳ ከተማሪፖርትቅዱስ ጊዮርጊስየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሪፖርት | ቅ/ጊዮርጊስ አሁንም ከሜዳው ውጪ ድል ማስመዝገብ አልቻለም።

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 7ኛ ሳምንት ላይ የደረሰ ሲሆን በዚህ ዙርም በውድድር አመቱ ወጣ ገባ የሚል አቋም እያሳየ የሚገኘው ሀዋሳ ከተማ በሜዳው ሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በሊጉ ወጥ አቋም ማሳየት የተሳነውን ቅዱስ ጊዮርጊስን አስተናግዶ ያለግብ አቻ ተለያይቷል። በዘንድሮው የውድድር ዘመን ከሜዳው ውጪ ማሸነፍ የተሳነው ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁንም ድል ማድረግ ተስኖታል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በ6ኛው ሳምንት የአምናውን ሻምፒዮን መቐለ 70 እ. አስተናግዶ 2-1 ማሸነፉ ሲታወስ እና የቡድኑን ወሳኝ አጥቂ ሰልሀዲን ሰዒድ ከጉዳት ማግኘቱ እና ከአቤል ያለውን እና ጌታነህ ከበደ ጋር የፈጠረው ጥምረት ሲታይ የሀዋሳውን ጨዋታ በቀላሉ ያሸንፋል የሚል ግምት ነበር። ሆኖም ግን በተቃራኒው ሆኖ ከሜዳው ውጪ ግብ ሳያስቆጥር ተመልሷል። ከቦታው ባገኘነው መረጃ መሰረት ቅዱስ ጊዮርጊስ ተደጋጋሚ እድሎችን መፍጠር ቢችልም ሳይጠቀምበት ቀርቶ በአቻ ውጤት ተመልሷል።

ውጤቱንም ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ መሪዎቹ ጎራ በደምብ መጠጋት የሚችልበትን አጋጣሚ ሲያመክን ሀዋሳ ከተማም በተመሳሳይ እድሉን አምክኗል። በ7ሳምንታት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመሪው ወልዋሎ አ.ዩ. በ4ነጥቦች ርቆ በ10 ነጥቦች 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሀዋሳ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በ1ነጥብ ዝቅ ብሎ በ9ነጥቦች 9ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።

ሊጉን ወልዋሎ አ.ዩ. በ14 ነጥቦች ሲመራ መቐለ 70 እ. እና ፋሲል ከተማ በቅደም ተከተል በ13 እና በ12 ነጥቦች 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። የኮከብ ግብ አግቢነቱን ደግሞ የፋሲል ከነማው ሙጂብ ቃሲም በ7 ግቦች ቀዳሚ ሲሆን የባህርዳር ከነማው ፍፁም ዓለሙ በ6 እንዲሁም የመቐለ 70 እ. አማኑኤል ገ/ሚካኤል በ5ግቦች ተከታዩን ደረጃ ይዘዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...