መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ማሊያዊው አጥቂ ሲዲ ኬታ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተለያይተዋል
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎች

ማሊያዊው አጥቂ ሲዲ ኬታ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተለያይተዋል

አጋራ
አጋራ

ማሊያዊ ሲዲ ኬታ በፈረሰኞቹ ቤት የሚጠበቀውን ያህል ግልጋሎት ባለመስጠቱ ከ4 ወራት ቆይታ በሇላ ከክለቡ ጋር በስምምነት ተለያይቷል፡፡

ፈረሰኞቹ ከዩጋንዳው ኬሲሲኤ ጋር ለነበራቸው የካፍ ቻምፒዬንስ ሊግ ቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ካምፓላ ሲያቀኑ ከጨዋታው መልስ ክለቡ ተጨዋቾችን ሊያሰናብት እንደሚችል መነገሩ የሚታወስ ሲሆን ከክለቡ ጋር በስምምነት የተለያየው የመጀመሪያው ተጨዋች ኬታ ቢሆንም ከክለቡ ጋር ሊለያዩ የሚችሉ ተጨዋቾች ስለመኖራቸው ክለቡ በይፋ ባያሳውቅም እየተነገረ ነው፡፡

ፈረሰኞቹ ተጨዋቹን በ2 ዓመት ኮንትራት ውል ጥቅምት 2010ዓ/ም ሲያስፈርሙት በኢትዮጵያ ኘሪሚዬር ሊግ ውድድር ባለፈም ኢትዮጵያን በመወከል በሚሳተፉበት የአፍሪካ መድረክ ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን ነበር፡፡ነገር ግን ፈረሰኞቹ ዘንድሮ በአፍሪካ ቻምፒዬንስ ሊግ ያሰቡትን ያህል ሳይጓዙ በዩጋንዳው ኬሲሲኤ በጊዜ ተሸንፈው ሲወጡ በፕሪሚየር ሊጉም ቢሆን ውጤታማ ናቸው ለማለት እስካሁን ያስመዘገቡት ውጤት አያስደፍርም፡፡

ተጨዋቹ ከክለቡ ጋር በነበረው የአጭር ጊዜ ቆይታም ቢሆን ተቀይሮ በተጫዎተባቸው የሊግ ጨዋታዎች ክለቡ ከሱ የሚፈልገውን ግልጋሎት መስጠት ባለመቻሉ የነበራቸውን የ2 ዓመት ኮንትራት ውል በስምምነት በማቋረጥ መለያዬታቸውን ክለቡ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ የገለፀ ሲሆን ተጨዋቹ ስለነበረው ቆይታ በማመስገን በሄደበት መልካም ነገር እንዲገጥመው ተመኝተዋል ፡፡

Photo credit-st George official page

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...