መነሻ ገጽ የዝውውር ዜናዎች ሙከራ |ፋሲልከተማ ሁለት የውጪ ተጨዋቾችን ለሙከራ አስመጥቷል
የዝውውር ዜናዎችፋሲል ከተማ

ሙከራ |ፋሲልከተማ ሁለት የውጪ ተጨዋቾችን ለሙከራ አስመጥቷል

አጋራ
አጋራ

የፋሲል ከተማ እግር ኳስ ክለብ በቀጣይ አመት ተጠናክረዉና ተፎካካሪ ሁኖ ለመቅረብ በዝዉዉር ገበያው ላይ በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ 
አፄዎቹ እስካሁን 6 ያህል የሀገር ዉስጥ ተጫዋቾችን ያስፈረሙ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ የዉጭ ተጫዋቾች ዝዉዉር ነሐሴ 25 መከፈቱን ተከትሎ ክለቡ በዛሬዉ እለት የኡጋንዳ ዜግነት ያለዉን ሮበርት ሴንቴንጎ እና ናይጄሬያዊዉን ክርስቶፈር አሞሶቢ ለሙከራ ክለቡን ተቀላቅለዋል፡፡ 

ሁለቱም ተጫዋቾች የፊት አጥቂ ሚና ያላቸዉ ተጫዋቾች ሲሆኑ ሴንቴንጎ ከዚህ ቀደም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ለሁለት አመታት መጫዎት ችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ተጫዋቹ በአሰልጣኝ ሚቾ በሚመራዉ የዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድን አባል የነበረና የኡጋንዳ ፕሪምየር ሊግን ለ4 አመት ያህል በከፍተኛ ጎል አስቆጣሪነት ማጠናቀቅ የቻለ ተጫዋቾች ነዉ፡፡ ቁመተ ለግላጋዉ ክርስቶፈር በበኩሉ በተለያዩ ሊጎች በፊት አጥቂነት እና በመስመር አማካይነት ተጫዉቷል፡፡ እኛም ክለባችን ለተቀላቀሉት አዲስ ተጫዋቾች እንኳን ደህና መጣህ እያልን መልካም ጊዜን እንድታሳልፉ እንመኛለን፡፡ 

አፄዎቹ የመጀመሪያ ግብ ጠባቂን ጨምሮ ሌሎች ተጫዋቾችን ወደ ቡድናቸዉ የቀላቀሉ ሲሆን ከታዳጊ ቡድኑ ደግሞ 5 ያህል ወጣት ተጫዋቾችን በክለቡ አካትተዋል፡፡ 

source-offical fasil kenema fb page

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂ አስፈረመ

መሳይ አያኖ አዲሱ የኢትዮጵያ ቡና የግብ ዘብ ሆኗል። በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሚሳተፈው...

አርሲ ነገሌዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ነገሌ አርሲ በነፃ ዝውውር ናይጄሪያዊ አጥቂ አግኝቷል

በኢራቅ ሊግ ቆይታ የነበረው አጥቂ ነገሌ አርሲን ይቀላቀላል። ኪቲካ ጀማን በዝውውሩ የመዝጊያ...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

መቐለ 70 እንደርታ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ

መቐለ 70 እንደርታ ክለብ የሌለውን አጥቂ ወደ ክለቡ አምጥቷል። በአሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም...

መቐለ 70 እንደርታኢትዮጵያ መድህንዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ጋናዊው ተጫዋች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ለመድን ፈረመ

ኢትዮጵያ መድን የአጋማሹን አራተኛውን ፈራሚ አግኝቷል። በአሰልጣኝ ገብረመድኅን ሐይሌ የሚመሩት የወቅቱ የሊጉ...