መነሻ ገጽ መከላከያ መከላከያ ከሰበታ ጋር በስምምነት የተለያዩትን አሰልጣኝ ስዩም ከበደን በኃላፊነት ሿሟል
መከላከያሰበታ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

መከላከያ ከሰበታ ጋር በስምምነት የተለያዩትን አሰልጣኝ ስዩም ከበደን በኃላፊነት ሿሟል

አጋራ
አጋራ

በመጀመሪያው ዙር የኢትዬጵያ ኘሪሚየር ሊግ ውጤት አልባ ጉዞ በማድረግ በ15 ነጥብ በደረጃ ሰንጠረዡ ወራጅ ቀጠናውን ተጠግተው በ13ኛነት ያጠናቀቀው መከላከያ አሰልጣኝ ምንያምር ፀጋዬን ካሰናበተ በሇላ በምትኩ አሰልጣኝ ስዩም ከበደን መቅጠሩ ታውቋል ፡፡
 ከሰበታ ከተማ ጋር የቆዩት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ክለቡን ወደ ኘሪሚዬር ሊጉ ያሳድጉታል ቢባልም በጉዞ ላይ እያሉ መለያየታቸው ታውቋል፡፡አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ከዚህ ቀደም በኘሪሚዬር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣አዳማ ከተማ፣የመኑንን ክለብ (አል-ሳክር) ባለፈው አመት አዲስ አበባ ከተማን ማሰልጠናቸው  ይታወሳል፡፡
በውጤት ማጣት ላይ ያሉት መከላከያዎች የመውረድ ስጋት የተጋረጠባቸው ሲሆን ክለቡን ከመውረድ ሊታደገው የሚችለው ሁነኛ አሰልጣኝ ስዩም ስለመሆኑ የተማመኑ ይመስላሉ፡፡አሰልጣኙና ክለቡ ስምምነት ላይ በመድረሳቸው መከላከያን በሁለተኛው ዙር ይዘው እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።   

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...