ለኳታር 2022 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ ተደረገ
በ2022 ኳታር ለምታዘጋጀው የዓለም ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ከሌሴቶ ጋር ነሐሴ 29 ቀን እና ጳጉሜ 3 ቀን በደርሶ መልስ ለሚደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል።
ከ24ቱ ተጫዋቾች በተጨማሪ በኖርዌይ አንደኛ ዲቪዚዮን የሚጫወቱት ሁለት ተጫዋቾች ማለትም ስትሮምጎድሴት እግር ኳስ ክለብ በግብ ጠባቂነት የሚጫወተው ዳንኤል ንጉሴ እና በሳርፕስበርግ እግር ኳስ ክለብ የአማካይ አጥቂ በመሆን ሚጫወተው አሚር አስካር እንዲሁም በጀርመን ሁለተኛ ዲቪዚዮን በሚገኝ ክለብ በተከላካይ ስፍራ ሚጫወተው ካሊድ ሙሉጌታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ጥሪ እንደተደረገለቻው ታውቋል፡፡
ግብ ጠባቂዎች
1 ጀማል ጣሰው – ፋሲል ከነማ
2 ምንተስኖት አሎ – ባህር ዳር ከተማ
3 ለዓለም ብርሃኑ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
ተከላካዮች
4 አስቻለው ታመነ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
5 ያሬድ ባዬ – ፋሲል ከነማ
6 አንተነህ ተስፋዬ – ድሬዳዋ ከተማ
7 ረመዳን የሱፍ – ስሁል ሽረ
8 አምሳሉ ጥላሁን – ፋሲል ከነማ
9 አህመድ ረሽድ – ኢትዮጵያ ቡና
10 ደስታ ደሙ – ወልዋሎ
11 ዮናስ በርታ – ደቡብ ፖሊስ
አማካዮች
12 ጋቶች ፓኖም – አልጉዋና
13 አማኑኤል ዮሃንስ – ኢትዮጵያ ቡና
14 ከነዓን ማርክነህ – አዳማ ከተማ
15 ሀይደር ሸረፋ – መቐለ 70 አንድርታ
16 ሽመልስ በቀለ – አልመካሳ
17 ታፈሰ ሰለሞን – ሐዋሳ ከተማ
18 ሱራፌል ደኛቸው – ፋሲል ከነማ
አጥቂዎች
19 አማኑኤል ገ/ሚካኤል – 70 እንድርታ
20 ዑመድ ኡክሪ – አልሱሙማ
21 ቢኒያም በላይ – ሱሪያንስ
22 አዲስ ግደይ – ሲዳማ ቡና
23 ሙጅብ ቃሲም – ፋሲል ከነማ
24 መስፍን ታፈሠ – ሐዋሳ ከተማ
ለቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች የካቲት 14/2011ዓ.ም ከጥዋቱ 3ሰዓት በሸበሌ ሆቴል ሪፖርት እደሚያደረጉ ታውቋል።
አስተያየት ይስጡ