በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣እንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር እና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር አማካኝነት ተዘጋጅቶ ለከፍተኛ ሊግ ክለቦች አሰልጣኞች ከሰኞ ጥር 18/2012ዓ.ም ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዛሬው እለት ጥር 22/2012ዓ.ም ተጠናቀቀ።

ስልጠናው ከእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር በመጡ አሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን ስልጠናው በክፍል ውስጥ የንድፈ ሀሳብ ትምህርት እና በሜዳ ተግባራት የታገዘ ነበር፡፡
በስልጠናው ወቅት የብሪቲሽ ኢምባሲ አምባሳደር በአዲስ አበባ ስታዲየም በመገኘት የስልጠናውን ሂደት በመከታተል ሰልጣኞችን አበረታተዋል።
እንዲሁም በትናንትናው እለት ጥር 21/2012ዓ.ም አምባሳደሩ ሰልጣኞችን ብሎም ሌሎች እንግዶችን በኢንባሲያቸው በመጥራት የኮክቴል ግብዣ በማድረግ ስልጠናው ቀን ከመጠናቀቁ አስቀድሞ የተሳትፎ የምስክር ወረቀት ለሰልጣኞች ሰተዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአምባሳደሩ ያዘጋጀውን የብሄራዊ ቡድን ማለያ በስጦታ መልክ የኢ.እ.ፌ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የህክምና ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዘሪሁን ቀቀቦ በማበርከት መሰል የስልጠና ግንኙነቶች መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸው ስልጠናውን ለሰጡት አሰልጣኞች እና ለእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር ምስጋናቸውን ገልጸዋል።

ሰልጣኞቹም ለአሰልጣኝ መምህሮቻቸው የኢትዮጵያ ባህላዊ አልባሳትን በስጦታ ያበረከቱ ሲሆን፤ አሰልጣኞቹም ከእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር የማህበሩ አርማ የታተመበትን ኳስ በስጦታ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አበርክተዋል።
አስተያየት ይስጡ