መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ከብራዚል ኤምባሲ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ከብራዚል ኤምባሲ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ከብራዚል ኤምባሲ አምባሳደር ሉዊስ ኤድዋርዶ ደ አጉኤር ቪላሪኒሆ ጋር በእግር ኳስ ልማት ላይ በጋራ በሚሰሩበት ሁኔታ ዙሪያ ትላንት ጥር 21/2012 ተወያዩ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከ ብራዚል እግር ኳስ ማህበር ጋር በጋራ መስራት በሚችሉበት እንዲሁም በብራዚል የሚገኙ ትልልቅ ክለቦች በኢትዮጵያ የእግር ኳስ አካዳሚ በሚከፍቱበት እና ኢትዮጵያዊያን የእግር ኳስ አሰልጣኞች ከብራዚል አሰልጣኞች ልምድ በሚወስዱበት እና ተጨማሪ የአሰልጣኝነት ስልጠናዎችን በሚያገኙበት ሀሳቦች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን፤ የብራዚል የእግር ኳስ ልማት ስትራቴጂ ምን እንደሚመስል እና ልምድ በሚገኝበት ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

የፍላሚንጎ እግር ኳስ ክለብ ቀደኛ ደጋፊ መሆናቸውን የገለጹት የብራዚል ኤምባሲ አምባሳደር ሉዊስ ኤድዋርዶ ደ አጉኤር ቪላሪኒሆ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ በፓርላማ ባአንድ ወቅት ያደረጉት ንግግርን በጋዜጣ ባነበቡት ጊዜ ኢትዮጵያን በምን መልኩ ማገዝ እንዳለባቸው ሲያስቡ መቆየታቸውን ለኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ገለጸውላቸዋል።
በቀጣይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ የጋራ እቅድ እንዲዘጋጅ እና የማቴሪያልም ሆነ የስልጠና እገዛ በሚደረግበት ዙሪያ ወደፊት እንደሚማከሩ ገልጸው ውይይታቸው ተጠናቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...