የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን (ዋልያዎቹን) የሚያሰለጥን አሰልጣኝ ለመመረጥ 7 የምርጫ መስፈርት በማዉጣት አሰልጣኛችን ለዉድድር መጋበዙ ይታወቃል ።
እስከአሁን ባለዉ መረጃ መሠረት ወዶ 12 የሚጠጉ አሰልጣኞች ብ/ቡድኑን የማሰልጠን ፍላጎት እንዳላቸው በኢሜይል እና በአካል ተገኝተው ካስገቡት ደብዳቤ ለማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ብ/ቡድኑን ለማሰልጠን ካመለከቱት አሰልጣኞች መካከል የዉጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኞች እንደሚገኙበት ምንጮች ጠቁመው ትልቅ ስም ያላቸው አሰልጣኞች እስከ አሁን ድምፃቸውን ማጥፋታቸው አነጋግሯል።የኢትዮጵያ ብ/ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆኖ ለሚሆነው አሰልጣኝ ዝቅተኛው 50 ሺህ ከፍተኛው 85 ሺህ ሊሆን እንደሚችል እየተነገረ ነው ።
አስተያየት ይስጡ