መነሻ ገጽ ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ ለህትመት ሰኞ ዕለት ማተሚያ ቤት የገባችው ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1440ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለች በበዓሉ ምክንያት የእዚህ ሳምንት እትሟን በነገው ዕለት በገበያ ላይ ታውላለች፡፡
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

ለህትመት ሰኞ ዕለት ማተሚያ ቤት የገባችው ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1440ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለች በበዓሉ ምክንያት የእዚህ ሳምንት እትሟን በነገው ዕለት በገበያ ላይ ታውላለች፡፡

አጋራ
አጋራ

ለህትመት ሰኞ ዕለት ማተሚያ ቤት የገባችው ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1440ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለች በበዓሉ ምክንያት የእዚህ ሳምንት እትሟን በነገው ዕለት በገበያ ላይ
ታውላለች፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ለገበያ ነገ ስትበቃም ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን? በሀገር ውስጥ ዘገባዋ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድርን አስመልክቶ ሊጉን ከሚመራው የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ቡድን ተጨዋቾች መካከል ስለክለባቸው ውጤታማነት እና ሌሎችን ጉዳዮች በማንሳት ጠንካራ ተጨዋቻቸውን ሽመክት ጉግሳን በተለያዩ ጥያቄዎች ዙሪያ አናግረነው ምላሽን ሰጥቷል፤ ሀትሪክ ከዛ ውጪ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እሁድ ዕለት መካሄድ ስለነበረበት እና ሳይካሄድ ስለቀረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የኢትዮጵያ ቡናና የመቐለ 70 እንደርታ ጨዋታና ግጥሚያው አዳማ ላይ በዝግ ስታድየም ይካሄዳል ስለመባሉና ቡና ስለሰጠው መልስ እንደዚሁም ደግሞ እየተባባሰ ስለመጣው የስፖርታዊ ጨዋነት ጥሰት ዙሪያ ዘገባ አላት፡፡
ሀትሪክ ሌላው ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት THE BIG INTERVIEW አምዷ የሲዳማ ቡናውን አሰልጣኝ ዘርኃይ ሙሉን በተጨዋችነት ዘመኑ ስለነበረው የስፖርት ህይወት፣ ስለስልጠና ዘመኑ፣ በአሁን ሰዓት ስላለው ስለ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ችግሮች እንዲሁም ሌሎችም ጥያቄዎች ቀርቦለት ለጋዜጣው ምላሹን ሰጥቶበታል፡፡
ሀትሪክ ስፖርት በባህር ማዶ የነገ ዘገባዋም የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታን አስመልክቶ ስለ ባለ ድሉ ሊቨርፑል እና ስለ ቡድኑ ተጨዋች ሞ.ሳላ እንደዚሁም ደግሞ ቼልሲ በድል ስላጠናቀቀው እና የሀዛርድ ምሽት ስለተባለበት የአውሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ሀትሪክ በጥሩ ዘገባዋ ታስነብቦታለች፡፡
የነገዋ ሀትሪክ አታምልጦት ከዛ ውጪም ሌሎች ያልተሰሙ ዘገባዎችን ሀትሪክ ነገ ማለዳ ይዛ እጅዎ ትገባለች፡፡
የሀትሪክን ትኩስ የሆኑ መረጃዎቿን ከጋዜጣዋ በተጨማሪ በርካታ ተከታታዮች ባሏት hatricksport.com ድረ-ገፃችን ላይም ያገኛሉ። ይጎብኙን፡፡
የሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የነገው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል፡፡
መልካም ንባብ

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣዜና እረፍትዜናዎች

የጋዜጠኛ መሸሻ ወልዴ አጭር የህይወት ታሪክ

ጋዜጠኛ መሸሻ ወልዴ ከእናቱ ከወ/ሮ ጌጤ ገ/ስላሴ እና ከአባቱ ሀምሳ አለቃ ወልዴ...

ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

ሀትሪክ አሁንም ቀጠሮ ማክበር ስልጣኔ ነው በሚለው አቋሟ ጸንታለች

ቅዳሜ ጠዋት በቀጠሮ  ቀናችን  እርስዎ ጋዜጣዋን በእጅዎ ያስገቡ እንጂ አዳዲስና ያልተሰሙ መረጃዎችን...

ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣዜናዎች

ሀትሪክ አሁንም ቀጠሮ ማክበር ስልጣኔ ነው በሚለው አቋሟ ጸንታለች

ቅዳሜ ጠዋት በቀጠሮ  ቀናችን  እርስዎ ጋዜጣዋን በእጅዎ ያስገቡ እንጂ አዳዲስና ያልተሰሙ መረጃዎችን...