ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከኤ.ዱ.ዩ ኮሚዩኒኬሽን ጋር በመተባበር ዘመናዊ የሆነ ድህረገፅ በመስራት ዛሬ ፕላኔት ሆቴል ላይ ባዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ አስመርቋል።
በኤ.ድ.ዩ ኮሚኒኬሽን የተሰራው የኦንላይን ድህረገፅ የተለያዩ ስራዎችን በቀላሉ ክለቡ እንዲያካሂድ ከማስቻሉ በተጨማሪ የክለቡ የገቢ ምንጭም ይሆናል።ድህረገፁ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል የማልያ ሽያጭ፣የስታድየም ትኬት ሽያጭ፣ደጋፊዎች የክለቡ አባል ማድረግ፣የገንዘብ መዋጮ እና ሌሎች ግልጋሎቶችን የሚሰጥ መሆኑን በጋዜጣዊው መግለጫ ላይ ተገልፆል ።