By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ወንድማማቾች ደርቢ በአቻ ዉጤት ሲጠናቀቅ ፤ በተመሳሳይ አዳማ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማም ጨዋታቸዉን በአቻ ዉጤት ደምድመዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችድሬዳዋ ከተማባህርዳር ከተማአዳማ ከተማፋሲል ከነማ

ወንድማማቾች ደርቢ በአቻ ዉጤት ሲጠናቀቅ ፤ በተመሳሳይ አዳማ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማም ጨዋታቸዉን በአቻ ዉጤት ደምድመዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አራተኛዉ ሳምንት የመጀመሪያ ዕለት ጨዋታ በወንድማማቾች ደርቢ ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።

በተመጣጣኝ የሜዳ ላይ ፉክክር ቀን 9:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ ጨዋታ ባህርዳር ከተማዎች የመጀመሪያ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። በዚህም ከግራ መስር በኩል ፍራኦል መንግስቱ ያሻማትን ኳስ አጥቂዉ ሀብታሙ ካበረደ በኋላ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ግን ለጥቂት ወጥታለች።

በአጠቃላይ በሙከራ ረገድ ቀዝቃዛ በነበረዉ የመጀመሪያዉ አጋማሽ ከዚች የባህርዳር ከተማ ተጠቃሽ ሙከራ በኋላ አፄዎቹ በአጥቂዉ ፍቃዱ አለሙ አማካኝነት ጥሩ የግብ ዕድል መፍጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ተጫዋቹ ኳሷን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሉ ምክንያት ጨዋታዉን መምራት የሚችሉበትን ግብ ሳያገኙ ቀርተዋል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ አፄዎቹ በይበልጥ በኳስ ቁጥጥሩ የተሻሉ ሁነዉ የተስተዋሉ የነበሩ ቢሆንም ነገር ግን ያን ያህል እምብዛም ተጠቃሽ ሙከራን ሁለቱም ክለቦች ሳያደርጉ አጋማሹ ተጠናቋል።

- ማሰታውቂያ -

በሁለተኛዉ አጋማሽም በተመሳሳይ አፄዎቹ የተሻለ መንቀሳቀስ የቻሉ ቢሆንም ነገር ግን አሁንም ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ ቡድን ሶስተኛዉ የሜዳ ክፍል ደርሰዉ አደጋዎችን በመፍጠር ረገድ ተዳክመዉ ተመልክተናል። በተቃራኒው ምንም እንኳን በኳስ ቁጥጥሩ መጠነኛ ብልጫ ይወስድባቸዉ እንጅ አደጋዎችን በመፍጠር ረገድ የተሻሉ የነበሩት የጣና ሞገዶቹ በሀብታሙ ታደሰ እና ተቀይሮ የገባዉ ወንድወሰን ጥሩ ጥሩ አንድ ሁለት ዕድሎችን ቢያገኙም መጠቀም ሳይችሉ ቀርተዉ ጨዋታዉ ያለ ግብ በአቻ ዉጤት ተጠናቋል።

አመሻሽ 12:00 በተደረገዉ ጨዋታ አዳማ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታቸዉን አንድ አቻ በሆነ ዉጤት አጠናቀዋል።

አመሻሽ 12:00 ሰዓት ሲል በዋና ዳኛ ዮናስ ካሳሁን መሪነት በጀመረዉ የአዳማ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች ወሳኟን ሶስት ነጥብ ለማግኘት ከነበራቸዉ ጉጉት አንፃር ጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር ብንመለከትበትም ነገር ግን ጨዋታዉ በሙከራ ረገድ ጥሩ ነበር ማለት አይቻልም። በዚህም በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ እምብዛም ሙከራዎችን ባላስመለከተን ጨዋታ በ26ተኛዉ ደቂቃ ላይ ቢኒያም አይተን በአዳማ በኩል ድንቅ ሙከራ ከሳጥን ዉጭ ቢያደርግም ነገር ግን ግብ ጠባቂዉ ዐብዩ ካሳየ ኳሷን ይዟል።

የሜዳዉን የኳስ ብልጫ ለመቆጣጠር ሰመጥሩ የነበሩት ድሬዳዋዎች በ30ኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ በአጥቂዉ ካርሎስ ዳምጠዉ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም ነገር ግን ግብ ማግኘት ሳይችሉ ቀርተዋል። አጋማሹ ሊጠናቀቅ የዳኛዉ ፊሽካ ሲጠበቅ አዳማዎች ግብ ለማስቆጠር ተቃርበዉ ነበር ፤ በዚህም ሱራፌል የግል ብቃቱ ተጠቅሞ ግብ ጠባቂዉን አታሎ ማለፍ ከቻለ በኋላ ኳሷን ወደ ግብ ልኳት የነበረ ቢህንም ነገር ግን ኳሷን መሐመድ አብዱለጢፍ ደርሶ አዉጥቷታል።

ከዕረፍት መልስ በተመሳሳይ እንቅስቃሴ በቀጠለዉ ጨዋታ በ58ተኛዉ ደቂቃ ላይ ድሬዳዋ ከተማዎች ፍፁም ቅጣት ምት አግኝተዉ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ያሬድ ታደሰ ኳሷን መትቷት ግብ ጠባቂዉ ይዟታል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታም በ78ተኛዉ ደቂቃ ላይ ቦና አሊ ያቀበለዉን ኳስ ፍቅሩ አለማየሁ ተጫዋቾችን አታሎ በማለፍ ጭምር ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

ብርቱ ፉክክር እየተደረገበት በቀጠለዉ ጨዋታ በ87ተኛዉ ደቂቃ ላይም ብርቱካናማዎቹ ከብዙ ጥረት በኋላ ተሳክቶላቸዉ የአቻነት ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም ከማዕዘን አሰጋኸኝ ያሻማዉን ኳስ እያሱ ለገሰ በግንባሩ ወደ ግብነት በመቀየር ጨዋታዉ አቻ እንዲጠናቀቅ አስችሏል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር :- የትግራይ ክለቦች ወደ ሊጉ እንዲመለሱ ፌዴሬሽኑ የሰጠውን ውሳኔ ጠቅላላ ጉባኤው እንዲመለከተው ወሰነ
Next Article የአዲስ አበባ ከተማ 18 ክለቦች ልዩነታቸውን ለመፍታት ያደረጉት ውይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችጅማ አባጅፋርየሊጉ ክለቦች ሲዳሰሱ

የጅማ አባ ጅፋር የመጀመሪያው ዙር ጉዞ ሲዳሰስ

ሚሊዮን ኃይሌ By ሚሊዮን ኃይሌ 6 years ago
ዋልያዎቹ ዝግጅታቸውን በካሜሩን ያደርጋሉ !!
የሀድያ ሆሳዕና ተጫዋቾች ልምምድ አቁመዋል
በኮንፌደረሽን ካኘ መከላከያ ያንግ ስፖርት አካዳሚን ይገጥማል
ሀትሪክ ስፖርትን ነገም ይጠብቋት ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገም በተለያዩ የሀገር ውስጥና የባህር ማዶ ዘገባዎቿ ከተፍ ብላ ለእርስዎ ውድና የተከበሩ አንባቢዋ ገበያ ላይ ትቀርባለች።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?