መነሻ ገጽ ሀትሪክ አበይት ጉዳዮች ሀትሪክ 12ኛ ሳምንት የክለቦች ውጤት ትንታኔ
ሀትሪክ አበይት ጉዳዮችዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሀትሪክ 12ኛ ሳምንት የክለቦች ውጤት ትንታኔ

አጋራ
አጋራ

 

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡና ላይ የግብ ናዳ አውርዶ ከረጅም ወራት በኋላ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 6-2 በማሸነፍ የሊጉን መሪነት ከመቐለ 70 እንደርታ በመረከብ ሊጉን በ23 ነጥብ መምራት የጀመረበትን ውጤት በዚህ ሳምንት አስመዝግቧል። በርካታ ተቃውሞችን እያስተናገደ የነበረው የፈረሰኞቹ አሰልጣኝ ሰርዳን ዥቪዥኖቭ ወደ ሊጉ መሪነት መመለሳቸው ትንሽ እፎይታን የፈጠረላቸው ይመስላል። ቅዱስ ጊዮርጊስም ከአንድ አመት በኋላ ነው የሊጉ መሪ መሆን የቻለው።


ወልቂጤ የአሸናፊነት ጉዞ

ክትፎዎቹ በተከታታ ሶስተኛ ድላቸውን ባህርዳር ከተማን 2-0 በማሸነፍ አስመዝግበዋል። በዚህም ደረጃቸውን በማሻሻል በ17 ነጥብ 5 ደረጃ ላይ መቀመት የቻሉበት ውጤት መሆን ችሏል።

 


ወላይታ ድቻ ድሬዳዋን በታሪኩ ማሸነፍ ችሏል

ከ2008 ጀምሮ ግንኙነት የጀመረው የሁለቱም ቡድኖች ጨዋታ። የጦና ንቦች በአንድም አጋጣሚ ቡርቱካናማዎቹን አሸንፈው የማያውቁ ሲሆን። በዚህ ሳምንት ግን 3 ግቦችን በማስቆጠር ግብ ሳይቆጠርበት በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ ታሪኩን ቀይሯል። በዚህ ጨዋታም የአመቱን ፈጣን ግብ በእዮብ አለማየሁ 48ኛው ሰከንድ ላይ ተቆጥራለች።


ኢትዮጵያ ቡና ወራጅ ቀጠና ውስጥ መገኘት

ድንቅ እንቅስቃሴን በማድረግ ጥሩ ውጤት ሲያስመዘግብ የነበረው ኢትዮጵያ ቡና ከቅርብ ጨዋታዎች ወዲህ ግን በተከታታይ ነጥብ ከመጣሉ ባሻገር ወራጅ ቀጠና ውስጥ መገኘቱ ግን ግርምትን ፈጥሯል። የቅርብ ጨዋታዎችን ስንመለከት ኢትዮጵያ ቡና ማግኘት ከነበረበት 9ነጥብ ሊያገኝ የቻለው 1 ነጥብ ብቻ ነው።

 


ሀድያ ሆሳዕና እና ሽንፈት አልላቀቅ ተባብለዋል

ጥሩ መነቃቃት ላይ የነበሩት ነብሮቹ አሁንም በድጋሚ በአመቱ መጀመሪያ የነበረቸው ተመሳሳይ የውጤት ማጣት ውስጥ ገብተዋል። ተከታታይ ሶስት ጨዋታዎችን በመሸነፍ መግኘት ከነበረባቸው 9 ነጥብ ምንም ያላሳኩት ነብሮቹ አሁንም ከሊጉ ግርጌ ፈቀቅ እንዳይሉ አድርጓቸዋል።

 


አዳማ ከተማ

ከተጫዋቾች ደሞዝ ክፍያ ተዳምሮ ውጤት ቀውስ ውስጥ ገብቶ የነበረው አዳማ ከተማ። አንፃራዊ መሻሻሎችን እያመጡ ቢሆንም በሜዳቸው ነጥብ መያዝ ቢችልም ከሜዳቸው ውጭ ያለው ነጥብ ጨዋታ ግን ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚገባ ነው።


ሀዋሳ ከተማ

ከሜዳው ውጭ ነጥብ ይዞ ለመመለስ እየተቸገረ ነው። በዚህ ሳምንትም በስሁል ሽረ 3-0 ሽንፈትን አስተናግዶ ተመልሷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...