ቅዳሜ ጠዋት በቀጠሮ ቀናችን እርስዎ ጋዜጣዋን በእጅዎ ያስገቡ እንጂ
አዳዲስና ያልተሰሙ መረጃዎችን ይዘናል
በሀገር ውስጥ ዘገባችን ሩቅ አላሚው የአዳማ ከተማ አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ እንግዳችን ነው “አሁን ወደምገኝበት ቦታ የመጣሁት በአቋራጭ ሳይሆን ብዙ ዋጋ ከፍዬ ነው” ብሏል። አሰልጣኝ ፋሲል ከሀትሪኩ ይስሃቅ በላይ ጋር በነበረው ቆይታ ስለ አሰልጣኞችና ወኪሎች እንዲሁም ዝውውር ላይ ስላለው ሸፍጥ አውግተዋል።
*….ዋሊያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫው ስለተደለደሉበት ጠንካራ ምድብና ሌሎች ጉዳዮች መረጃ ይዘናል…
- ማሰታውቂያ -
*…የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሙጂብ ቃሲምን ዝውውር አግዷል ሁለቱ ወገኖች ባስገቡት ደብዳቤ መሠረት ሙጂብ ከፋሲል ውጪ የትም አይጓዝም … ምናልባት ግን……?
*… የኦሎምፒክ ኮሚቴው ፕሬዝዳንት ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ኢቢሲን አብጠልጥለዋል…ስልጣኔንም አቅም ብለዋል…ኢቢሲም ዝምታን መርጧል…
*…ከመሸሻ ወልዴ ጋር ቆይታ ያደረጉት የባህርዳር ከተማው መናፍ አወልና የመከላከያው ገናናው ረጋሳ የሚሰማቸውን ተንፍሰዋል…
*…..በውጪ ሃገር ዘገባዎቻችን….
*…. የነጮቹ ሪያል ማድሪዶችን በር የሚጠብቀው ቲባውት ኩርቱዋ “ከሪያል ማድሪድ ጋር ታሪክ እየሰራው መቀጠል እፈልጋለሁ” ሲል ተናግሯል…….
*….. “ወደ ኦልድትራፎርድ ያቀናው ራፋኤል ቫራን “ጠንካራ ሰራተኛ ስራዬን የምወድና ህልመኛ ተጨዋች ነኝ” ሲል ተናግሯል…
*…ቸልሲን ከህልሙ ጋር ለማገናኘት ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ ዳግም የተመለሰው ሮሜሉ ሉካኩ “ወደ ቸልሲ የተመለስኩት ያልጨረስኩት የቤት ስራ ስላለኝ ነው” ብሏል…….
*…… የክርስቲያኖ ሮናልዶ ጉዳይ እያከራከረ ነው….የጁቬንቱስና የሮናልዶ ቆይታ አለየለትም…
*..ማርቲን ኦዲጋርድ ዳግም ወደ አርሰናል ተመልሷል…ግንኙነታቸው ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሻግሯል…….
*….የባሎን ደኦር አሸናፊ ማን ይሆን?የጣሊያኑ ኮከብ ጆርጂንሆ የባሎንዶር አሸናፊነት ይገባዋል? በዚህ ዙሪያ ዘገባ ይዘናል……..
እናም ሌሎች መረጃዎች….
እርስዎ ብቻ ቀጠሯችንን አክብረው ጋዜጣዋን በእጅዎ ያስገቡ እንጂ ተዝናንተው ቁምነገር የሚጨብጡበት አዳዲስ መረጃዎችንን የሚያገኙበት ይሆናል…..
ቅዳሜና እሁዳችሁ
የተባረከ ይሁን……


