ቅዳሜ ጠዋት በቀጠሮ ቀናችን እርስዎ ጋዜጣዋን በእጅዎ ያስገቡ እንጂ
አዳዲስና ያልተሰሙ መረጃዎችን ይዘናል
በሀገር ውስጥ ዘገባችን ፋሲል ከነማ የ2013 ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ባለቤት ሲሆን የአንበሳውን ድርሻ ከተወጡት መሃል አንዱ የሆነው የአመቱ ኮከብ ግብ ጠባቂ ሚካኤል ሳማኪ እንግዳችን ነው… በርካታ ጉዳዮችን ከተባባሪያችን ተሾመ ፋንታሁን ጋር ያወጋው ሳማኪ ” ኢትዮዽያ ውስጥ 80 በመቶ ደመወዝ መክፈል እንኳን አይችሉም የፋሲል ከነማ ተጨዋች ባልሆን ምርጫዬ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይሆን ነበር” ሲልም ተናግሯል። ሳማኪ
“ኢትዮዽያ ውስጥ ህልሜን አሳክቻለሁ በአፍሪካ መድረክ ከፋሲል ከነማ ጋር አዲስ ታሪክ ማጻፍ እፈልጋለሁ” ሲልም ተናግሯል።
*…..”ከእኛና ከጠራናቸው እንግዶች በላይ እግዚአብሄር እንዲከብር ነበር የፈለግነው…ደግሞም ተሳክቶልናል” ሲል አዲሱ ሙሽራ ምንተስኖት አዳነ ተናግሯል። ከዮሴፍ ከፈለኝ ጋር ቆይታ አድርጓል
- ማሰታውቂያ -
*….ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያቀናው ቡልቻ ሹራ በፈረሰኞቹ ቤት አዲስ ታሪክን ማጻፍ ያልማል።
*….እንየው ካሳሁን ፋሲል ከነማን ለቅቆ ድሬዳዋ ከተማን ተቀላቅሏል… ለምን ወጣ? በሚለው ጉዳይ ላይ ቅሬታውን የገለጸው እንየው “ለጎንደር ህዝብና ለፋሲል ደጋፊ ያለኝ ፍቅር የተለየ ነው፧ ፈልጌ ሳይሆን ተገፍቼ ነው የወጣሁት” ሲል ቅሬታውን ገልጿል…የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አብዮት ብርሃኑና ዋና አሰልጣኙ ስዩም ከበደን ምላሽ ይዘናል።
*…..በውጪ ሃገር ዘገባዎቻችን…..
*….አዲሱና አነጋጋሪ ስለሆነው የሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ ኮንትራት መረጃ ይዘናል…..
*….. ” ከአለማችን ምርጥ ክለቦች መሃል አንዱ ለሆነው ሊቨርፑል የመጫወት እድል ማግኘት የማይታመን ነው”ሲል አዲሱ ፈራሚ ኮናቴ የተናገረበትን ዘገባ ይዘናል….
*… ዳኒ አልቬዝ ” ብራዚልን በኦሎምፒክ መወከል መቻሌ አኩርቶኛል” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።
*……” በአርሰናል ማሊያ የመጀመሪያ ጨዋታዬን ለማድረግ ጓጉቻለሁ” ብሏል ኤምሬትስ የደረሰው አዲሱ መድፈኛ ሳምቢ ሎኮንጋ ….
*….በቶኪዮ ኦሎምፒክ በእግር ኳሱ ይደምቃሉ ስለተባሉት ኮከቦችም መረጃ ይዘናል…
እናም ሌሎች መረጃዎች….
እርስዎ ብቻ ቀጠሯችንን አክብረው ጋዜጣዋን በእጅዎ ያስገቡ እንጂ ተዝናንተው ቁምነገር የሚጨብጡበት አዳዲስ መረጃዎችንን የሚያገኙበት ይሆናል…..
ቅዳሜና እሁዳችሁ
የተባረከ ይሁን……


