ሀትሪክ ስፖርት በነገ እትሟ
ባለ ቀለሟ እና ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ ማክሰኞም ለንባብ ትበቃለች፤ አታምልጦት፡፡
ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን
በሀገር ውስጥ የሸገር ደርቢን አስመልክተን ከኢትዮጵያ ቡና እና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨዋቾች መካከል ሀብታሙ ታደሰን፣ ምንተስኖት አዳነን፣ ወንድሜነህ ደረጄን እና አስቻለው ታመንን አናግረናቸዋል፤ ደርቢውን ማን በአሸናፊነት ይወጣል? ለዛ ምላሽ አላቸው፡፡
ሀትሪክ ስፖርት በሌላ የሀገር ውስጥ እትሟ THE BIG INTERVIEW በሚለው አምድ የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ሚቾ ከጋዜጣው ለቀረበላቸው በርካታ ጥያቄ ምላሻቸውን ሰጥተውናል፡፡
ከእነዚህ መካከልም ከዚህ በታች ያሉት ይገኝበታል፡፡
“እኔ ራሴን የማየው የኢትዮጵያዊ ደም ያለው በአፍሪካ ውስጥ የሚኖር የሰርቢያ ድብ አድርጌ ነው” ሲሉ ሌላው ደግሞ
“እንደ አንድ የጊዮርጊስ ደጋፊ ይህ ያለውጤት ጉዞው ዘንድሮ ቢያበቃ ደስ ይለኛል” ያሉት ይጠቀሳል፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ከሀገር ውስጥ ባሻገር በባህር ማዶም የተለያዩ ዘገባዎችን የምታስነብቦት ይሆናል፡፡
ሀትሪክ የሊቨርፑልን አጥቂ መሐመድ ሳላን አስመልክቶ ራስ ወዳድ የምባል አይነት ተጨዋች አይደለውም ያለበት ሲጠቀስ ሽኮርዳን ሙስጣፊም ስለ አርሰናል የእግር ኳስ ህይወቱ ይናገራል፤ ሮሜሉ ሉካኮም ስለማንቸስተር ዩናይትድ፣ ኢንተር ሚላን እና ጆሴ ሞውሪኖ የሚላችሁ ይኖራል፤ ሀትሪክን አንብቧት ይደሰቱባታል፡፡
አስተያየት ይስጡ