መነሻ ገጽ ወልዋሎ ወልዋሎ አዲግራት 4 ተጫዋቾችን በይፋ አስፈረመ !
ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ወልዋሎ አዲግራት 4 ተጫዋቾችን በይፋ አስፈረመ !

አጋራ
አጋራ

በተቋረጠው የውድድር ዓመት ድንቅ ጅማሮን ማሳየት የቻሉት ቢጫ ለባሾቹ በዝውውር መስኮቱ ዘግየት ብለው ቢገቡም በዛሬው ዕለት አራት ተጫዋቾችን ማስፈረማቸው ታውቋል ።

ወልዋሎች በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂውን ወንድወሰን አሸናፊን ከስሑል ሽረ ለሁለት ዓመታት ሲያስፈርሙ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ቡና እና ወላይታ ድቻ ተጫውቶ ማሳለፉ የሚታወስ ነው ።

 

ፎቶ- ወንደሰን አሸናፊ በግራ | አወት ገ/ሚካኤል በቀኝ

ሌላኛው ስሑል ሽረን በመልቀቅ ቡድኑን መቀላቀል የቻለው ተጫዋች ዓወት ገብረ ሚካኤል ሲሆን በተለይም በጅማ አባጅፋር ስኬታማ ጊዜን አሳልፎ ማለፉ ይታወሳል ።

ወደ ኢትዮጵያ ቡና ካቀና በኋላ በውድድር ዓመቱ መጀመሪያ ላይ ድንቅ ብቃቱን በማሳየት በተመልካቹ ልብ ውስጥ ገብቶ የነበረው ዳንኤል ደምሱ የቢጫ ለባሾቹ ሌላኛው ፈራሚ ሲሆን መቐለ 70 እንደርታ ጋር በይፋ በመለያየት ለሁለት ዓመታት በወልዋሎ ቤት ለመቆየት ተስማምቷል ።

ፎቶ ከላይ – ዳንኤል ደምሱ | ከታች አስናቀ ሞገስ

አራተኛው የቢጫ ለባሾቹ ፈራሚ መሆን የቻለው ልምድ ያለው የመስመር ተጫዋቹ አስናቀ ሞገስ ሲሆን በተለይም የወልዋሎችን የመስመር ቦታ ክፍተት እንደሚሞላ ይጠበቃል ።

 

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...