በ33ኛዉ የካሜሩን የአፍሪካ ዋንጫ ከስምንት አመታት በኋላ ዳግም ተሳታፊ ለሆኑት ለዋልያዎቹ ባለሀብቱ አቶ ወርቁ አይተነው ዳጎስ ያለ የገንዘብ ሽልማት ለመሸለም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ዋልያዎቹ የሚገኙበት ምድብ ቀላል የሚባል ባይሆንም ጨዋታዎችን በድል ተወጥተው ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉ ከሆነ ለእያንዳንዳቸው በነፍስወከፍ አንድ መቶ ሺ ብር (100,000) ለመስጠት ቃል ገብተዋል። ባልሀብቱ ከቻሉም ወደስፍራው አቅንተው ለዋልያዎቹ ድጋፋቸዉን እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ዋልያዎቹ ከምድባቸው የሚያልፉ ከሆነ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር እንደሚሸልም መገለፁ ይታወሳል።
©Sportzone
አስተያየት ይስጡ