መነሻ ገጽ ከ 20 ዓመት በታች ሴቶች የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለአለም ዋንጫ ለማለፍ 180 ደቂቃ ብቻ ቀርቷቸዋል !!
ከ 20 ዓመት በታች ሴቶችዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለአለም ዋንጫ ለማለፍ 180 ደቂቃ ብቻ ቀርቷቸዋል !!

አጋራ
አጋራ

በ2022 የሴቶች ከ20 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማጣርያ አራተኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአበበ ብቂላ ስታዲየም የታንዛንያ ብሔራዊ ቡድንን 2ለ0 አሸንፈዋል።

አስቀድሞ ከሁለት ሳምንታት በፊት ዳሬሰላም ላይ በታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድን 1ለ0 ተሸንፈው የነበሩት የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት በመልሱ ጨዋታ ተጋጣሚያቸውን የታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድን በረድኤት አስረሳኸኝ ሁለት ጎሎች አሸንፈዉ ወደ አምስተኛው እና ወደ መጨረሻው ዙር ተሸጋግረዋል።

ለተከታታይ አስራ አንድ ጨዋታዎች ያህል ያለሽንፈት ተጉዞ የነበረዉ የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከሳምንታት በፊት ካጋጠመዉ ሽንፈት በማገገም በዛሬው ዕለት ወደ አሸናፊነት የተመለሱበትን ድልም ነዉ ያስመዘገቡት።

በቀጣይ በመጨረሻዉ የማጣሪያ ጨዋታ የጋናን እና ኡጋንዳ ብሔራዊ ቡድንን አሸናፊ የሚገጥሙ ሲሆን የደርሶ መልሱን ጨዋታ በድል የሚወጡም ከሆን ኮስታሪካ በምታዘጋጀው የ2022 የአለም ከ20 አመት በታች የሴቶች ዋንጫ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...