መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዱስ ጊዮርጊስ አራት አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈርሟል!!
ቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስ አራት አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈርሟል!!

አጋራ
አጋራ

በዘንድሮው የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ 3ኛ ደረጃን ይዘዉ ማጠናቀቅ የቻሉት ፈረሰኞቹ ዋና አሠልጣኝ ከመሾማቸው በፊት በዝውውር ገበያው ላይ በንቃት ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ። እስከ አሁን ድረስም ቸርነት ጉግሳን እና በረከት ወልዴን ማስፈረማቸዉ ይታወሳል።

አሁን ደግሞ ምኞት ደበበን ከሀዋሳ ከተማ ፤ቡልቻ ሹራ ከሰበታ ከተማ ፤ሱለይማን ሀሚድን ከሀድያ ሆሳዕና ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።

በአዳማ ከተማ ቤት ለአራት አመታት ያክል መጫወት የቻለዉ ተከላካዩ ባሳለፍነው የዉድድር አመት ወደ ሀዋሳ ከተማ አቅንቶ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ደግሞ ከቀጣዩ የዉድድር አመት ጀምሮ ለፈረሰኞቹ ለመጫወት ተስማምቷል።

ሌላኛዉ ለክለቡ ፊርማዉን ያኖረዉ ቸጫዋች ደግሞ ወጣቱ የመስመር አጥቂ ቡልቻ ሹራ መሆኑ ታዉቋል። ከክለቡ ሰበታ ከተማ ጋር ድንቅ የዉድድር አመትን ያሳለፈዉ የመስመር ተጫዋቹ ዛሬ ረፋድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ፊርማዉን ማኖሩ ተረጋግጧል።

በተያያዘም ግዙፋ አማካኝ ጋቶች ፓኖም ፈረሰኞቹን መቀላቀሉ ዛሬ በይፋ ተረጋግጧል። አማካኙ በዉድድር አመቱ ግማሽ ላይ ወላይታ ዲቻን ተቀላቅሎ የነበረ ሲሆን ነገር ግን ቆይታዉ ከግማሽ አመት በላይ ሊዘልቅ አልቻለም ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ቡና ቤት መጫወት የቻለዉ ጋቶች አሁን ላይ በይፋ የፈረሰኞቹ መቀላቀሉ ተረጋግጧል።

ሌላኛዉ በፈረሰኞቹን መለያ በቀጣዩ የዉድድር ዓመት የምንመለከተዉ ተጫዋች ደግሞ የመስመር ተከላካዩ ሱሌይማን ሀሚድ መሆኑ ተረጋግጧል። ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ያለውን ውል ያጠናቀቀው ሱለይማን ሀሚድ ቅዱስ ጊዮርጊስን የተቀላቀለ 6ኛዉ ተጫዋች ሆኖአል።

በተጨማሪም አዳዲስ ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊሶች የሳልሀዲን ባርጌቾ ፤ናትናኤል ዘለቀ፤ደስታ ደሙ፤ሀይደር ሸረፋ እና አማኑኤል ገ/ሚካኤልን ዉል ለተጨማሪ አመት ማራዘማቸዉ ተሰምቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...