በዮሴፍ ከፈለኝ
የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ ተጥሎባቸዋል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ የሆኑትን የቀድሞውን ኢንተርናሽናል ዳኛ ክንዴ ሙሴን ማገዱ ታውቋል።

ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ በረዳት ዳኝነቱ የሚታወቀው የአሁኑ የሊጉ መሪ የቡድን መሪ ክንዴ ሙሴ በፕሪምየር ሊጉ ሲዳማ ቡና በሚያደርጋቸው ጨዋታዎችጨየዳኝነት ምደባን ቀድሞ ማወቁና መረጃውን ያቀበለውን የኮሚቴ አባል ወይም ሌላ ባለሙያን ስም አጋልጥ ሲባል ፍቃደኛ ባለመሆኑ ከቡድን መሪነቱ መታገዱን የደረሰን መረጃ ያስረዳል።
ከሁለት አመት በፊት ከዳኝነት አለም የተሰናበተው እና ባለፈው አመት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን የብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ አባል እና የፊዚካል ኢንስትራክተር ሆኖ ያገለገለው ክንዴ ከሌላው ወገን የተሻለ መረጃ የማግኘት ዕድል ቢፈጥርም አወዳዳሪ አካሉ ምንጩን ባለመግለፁ እርምጃ መውሰዱ ታውቋል። በቀጣይ የሊጉ ፉክክር ላይ ጥያቄ እንዳይፈጥር አወዳዳሪ አካሉ ከብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ አመራሮች ጋር ጠንከር ያለ ውይይት ማድረግ እንደሚጠበቅበት ይታመናል።
ሲዳማ ቡና በሊጉ የ28ኛ ሳምንት መርሀግብር ዛሬ ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በአቤል ያለው ሁለት ጎሎች 2ለ0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።
አስተያየት ይስጡ