መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ የሰበታ ከተማ ተጫዋቾች ልምምድ አቁመዋል
ሰበታ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሰበታ ከተማ ተጫዋቾች ልምምድ አቁመዋል

አጋራ
አጋራ

የሰበታ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በአሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው እየተመራ በመጀመሪያው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ካደረጋቸው አስራ አምስት ጨዋታዎች በአንዱ አሸንፎ በስድስት አቻ ተለያይቶ እንዲሁም በስምንት ጨዋታዎች ተሸንፎ በደረጃ ሰንጠረዡ ግርጌ ላይ መቀመጡ ይታወቃል ።

ከአስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ ስሙ ይነሳ የነበረው ይህ ክለብ በህዳር 24 / 2014 ዓ.ም ከአስር የክለቡ ተጫዋቾች ከደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ክፍያ ጋር በተያያዘ ቅሬታ ቀርቦበት ነበር ። ክለቡ ከእረፍት መልስ ለሁለተኛው ዙር ዝግጅት ለማድረግ በትላንትናው ዕለት የተሰባሰበ ቢሆንም ተጫዋቾቹ ልምምድ ለመስራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ዝግጅታቸውን መጀመር ሳይችሉ ቀርተዋል ለዚህም እንደ ምክንያት የቀረበው አስራ አንድ ተጫዋቾች የ2013 ዓ.ም የአራት ወራት የደመወዝ እና የጥቅማ ጥቅም ክፍያ እንዲሁም በያዝነዉ የውድድር አመት ደግሞ ለሁሉም የክለቡ ተጫዋቾች የሁለት ወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው ወደ ሶስተኛው ወር መቃረባቸው ነው ።

የ2013 የውድድር አመት ቀሪ ክፍቻዎች ያልተከፈላቸው እራ አንደለ ተጫዋቾች ቅሬታቸውን ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያስገቡት ሲሆን በቅሬታ ደብዳቤያቸው ላይ እንደገለፁት ከሆነም ክፍያዎችን በተገቢው ጊዜ ባለማግኘታቸው ምክንያት ቤተሰቦቻቸው ችግር ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል ። ስለሆነም ክለቡ ክፍያቸውን ፈፅሞላቸው ሙሉ ትኩረታቸውን በእግር ኳሱ ላይ እንዲያደርጉ እና ቤተሰቦቻቸውም ከገጠማቸው ችግር ማላቀቅ ይችሉ ዘንድ ጠይቀዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...