የዉድድር አመቱን በድሬዳዋ ከተማ ያሳለፈው ናሚቢያዊዉ አጥቂ ጁንያስ ናንጄቦ ሰበታ ከተማን መቀላቀሉ ተረጋግጧል።
በአሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራዉ እየተመሩ በዝዉዉር ገበያዉ ላይ በንቃት በመሳተፍ የተለያዩ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ በመቀላቀል ላይ የሚገኙት ሰበታ ከተማዎች በዛሬዉ ዕለት ደግሞ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቹን ጁንያስ ናንጄቦ ማስፈረማቸዉ ተሰምቷል።
የቀድሞዉ የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ተጫዋች የነበረዉ አጥቂዉ በተገባደደው የዉድድር አመት ወደ ድሬዳዋ ከተማ አምርቶ መልካም የሚባል አመትን ማሳለፉ አይዘነጋም።