አሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራዉን በዋና አሰልጣኝነት የቀጠሩት ሰበታ ከተማዎች አሁን ደግሞ ወደ ዝዉዉር ገበያዉ በመግባት የተለያዩ ተጫዋቾችን ወደ ቡድናቸዉ በመቀላቀል ላይ ይገኛሉ።
አሁን ደግሞ የቀድሞዉን የመከላከያ እና መቀለ 70 እንደርታ እንዲሁም የዉድድር አመቱን በአዳማ ከተማ ቤት ያሳለፈውን የመስመር ተከላካይ ታፈሰ ሰርካን ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።
ታታሪዉ የመስመር ተከላካይ ታፈሰ ሰርካ በዉድድር አመቱ ምንም ክለቡ አዳማ ከተማ ዉጤታማ መሆን ባይችልም በግሉ ጥሩ አመትን ማሳለፉ ይታወሳል።


