መነሻ ገጽ ባህርዳር ከተማ የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ ወደ አሸናፊነት ተመልሰዋል
ባህርዳር ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየጨዋታ ዘገባጅማ አባጅፋር

የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ ወደ አሸናፊነት ተመልሰዋል

አጋራ
አጋራ

በስድስተኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ጅማ አባጅፋርን የገጠመው ባህርዳር ከተማ በአሊ ሱሌይማን ሁለት ግቦች አሸንፎ ወጥቷል ።

ጅማ አባጅፋሮች በአምስተኛ ሳምንት ጨዋታ ከተጠቀመው ምርጥ 11 አራች ቅያሪዎችን ያደረጉ ሲሆን ሽመልስ ተገኝ ፤ አላዛር ሳሙኤል ፤ አሳሪ አልመሀዲንን እና መሀመድኑር ናስርን እንዲሁም ባህርዳር ከተማ በበኩሉ በረከት ጥጋቡን እና ኦሴ ማውሊን ወደ ቋሚ አሰላለፍ መልሰው ጨዋታቸውን ጀምረዋል ።

በጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች ከሽንፈት የመጡ እንደመሆናቸው ይህን ጨዋታ አሸንፈው ለመውጣት በሜዳ ላይ ብርቱ ትግል አድርገዋል ። በሁለቱም በኩል ከፍተኛ የማጥቃት እንቅስቃሴ የታየተበት ጨዋታ በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች በግብ ሙከራ ግን የታጀበ አልነበረም ።

በጨዋታው 18ኛ ደቂቃ ላይ ባህርዳር ከተማ በአሊ ሱሌይማን አማካኝነት የመጀመሪያውን ግብ አስቆጠሩ ። አማካዩ አለልኝ አዘነ በግራ መስመር ይዞት የገባውን ኳስ ለአሊ ሱሌይማን አቀብሎት አሊ ቀጥሩ አጨራረስ አስቆጥሮታል ።

ጅማ አባጅፋሮች ኳሱን ተቆጣጥረው የመጫወት ዝንባሌን ቢያሳዩም ወደ ፊት ለመሄድ የሚያደርጉት ጥረት ግን የተሳካ አልነበረም ። በአንፃሩ ባህርዳር ከተማዎች በፍጥነት ወደ ፊት በመሄድ ያደርጓቸው የነበሩ ጥረቶች የጅማ አባጅፋር የተከላካይ መስመርን የፈተኑ ነበሩ ። 28ኛው ደቂቃ ላይ ኦሴይ ማውሉ ከሳጥን ውጪ ወደ ግብ የሞከረው ኳስ በግብ ጠባቂው ተመልሷል ። በተመሳሳይ 38ኛ ደቂቃ ላይ አብዱልከሪም ኒኪማ ከሳጥን ውጪ የሞከረው ኳስ በግብ ጠባቂው አላዛር ተመልሷል ።

ሁለተኛው አጋማሽ በሁለቱም በኩል በመጀመሪያ አጋማሽ እንደነበረው በጥሩ ፉክክር ነቀጠለ ነበር ። ጨዋታውን እየመሩ የነበሩት የጣና ሞገዶቹ 50ኛ ደቂቃ ላይ መሪነታቸውን ያጠናከሩበትን ግብ አስቆጠሩ ። አብዱልከሪም ኒኪማ ያቀበለውን ኳስ ተጠቅሞ ኡሊ ሱሌይማን ሁለተኛውን ግብ ማስቆጠር ቻለ ።

በቀሩት ደቂቃዎች ጅማ አባጅፋሮች በተሻለ ለመንቀሳቀስ ቢሞክሩም በሶስተኛው የማጥቃት ዞን ሲገቡ የነበራቸው አጠቃቀም ደካማነት ግብ እንዳያስቆጥሩ አድርጓቸዋል ። ይባሱንም ባህርዳር ከተማዎች በፈጣን አጨዋወት ወደ ፋት በመሄድ ለግብ የቀረቡ ሙከራዎችን ማድረግ ችለው ነበር ። በተለይም በፍፁም አለሙ አማካኝነት የተፈጠሩ የግብ ዕድሎች መምከናቸው የጣና ሞገዶቹ መሪነታቸውን እንዳያሰፉ አድርጓቸዋል ።

በጨዋታው 83ኛ ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተሻገረውን ኳስ በላይ አባይነህ በግንባሩ ገጭቶ ለማስቆጠር ያደረገው ሙከራ ግብ ጠባቂው ፋሲል ገብረሚካኤል በድንቅ ብቃት ግብ ከመሆን አድኖታል ።

ውጤቱን ተከትሎም አሸናፊው ባህርዳር ከተማ ነጥቡን ወደ 10 ሲያሳድግ እስካሁን ምንም ማሸነፍ ያልቻለው ጅማ አባጅፋር ያለምንም ነጥብ የሊጉ ግርጌ ላይ ተቀምጧል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...